TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከስልጤ ዞን...

"ስልጤ ገርቤ በር የተጎዱ በርካታ #ፖሊሶች ጦራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልም መተዋል፡፡ እዛው ነው ምሰራው!"

#ቲክቫህኢትዮጵያ #tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1
ዶክተር ወርቁ በዳዳ ከታሰሩ 15 ቀን ሆኗቸዋል!

ነሃሴ 10 ቀን 2011 ዓ/ም ከመኖሪያ ቤታቸው የኦሮሚያ ፖሊስ እንደሆኑ በተነገረላቸው ሲቪል በለበሱ ሰዎች የተወሰዱት መምህሩ ዶክተር ወርቁ በዳዳ ከታሰሩ 15 ቀን እንደሆናቸው፤ እስካሁን ድረስም ለመታሰራቸው ምክንያት እንዳልቀረበ፤ ፍርድ ቤትም እንዳልቀረቡ ቤተሰቦቻቸው ለTIKVAH-ETH ተናግረዋል።

ከቤተሰቦቻቸው መካከል ለTIKVAH-ETH በስልክ የተናገሩት፦

"ነሃሴ 10 ቀን 2011 ዓ/ም - 7 ሰዓት ከቤት ሊወጣ ሲል ነው የመጡት፤ ሰቪል ለብሰው ነው የመጡት ከኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ነው የመጣነው ብለው ቤት ፈተሹ ከዛም ይዘውት ሄዱ። እስካሁን ይሄነው የሚባል ነገር አልተናገሩም፤ ቡራዩ ወረዳ 1 ፖሊስ ጣቢያ ነው ያስቀመጡት። ፍርድ ቤትም ቀርቦ ይሄን አጥፍተሃል የሚሉት ነገር የለም። ላፕቶፑ፣ ስልኩ ፣የሱም የባለቤቱም ሃርድዲስኮች፣ ካሜራ፣ፍላሽ.. የቀረ ነገር የለም ተወስዷል። አንድ ጊዜ ብቻ ለምርመራ ቀርበው አናግረውታል ከዛ በተረፈ የላፕቶፕና የሌሎች ሰነዶች ውጤቶች ስላልመጡን ነው ምክንያታቸው፤ 15 ቀን ሙሉ እንዲህ ነው ተብሎ ፍርድ ቤትም አልቀረበም፤ እንዲህ አጥፍተሃልም አልተባለም።"

እያያዛቸው እንዴት ነው?

"እዛ ያሉት #ፖሊሶች ጥሩ አመለካከት ነው ያላቸው፤ #ድብደባም ምንም ነገር አልተካሄደባትም። ግን ለምን አስረው እንዳስቀመጡት እኛም አልገባንም"

በስልክ ያናገርናቸው እኚሁ የዶ/ር #ወርቁ_በዳዳ ቤተሰብ ለበላይ አመራሮችም ጉዳዩን እንዲያብራሩ ቢጠይቁም ምላሽ እንዳላገኙ ተናግራዋል። የሚመለከተው አካል መፍትሄ እንዲሰጣቸውም ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia