TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አልሃምዱሊላሂ ~ #ድምፃችን ተሰማ

* 28 ጊዜያዊ የዑለማዎች አገዥ ምክር ቤት ተቋቁሟዋል
* 7 ጊዜያዊ አጋዥ ቦርድ አባላት ተመርጠዋል

ምስጋና ለአላህ፣ ምስጋና ለኮሚቴዎቻችን፣ ምስጋና ለሙፍቴ ሸህ ዑመር፣ ምስጋና ለጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ይሁንና ዛሬ ሕገ ወጡ መጅሊስ ከሥልጣን ወረደ የአመታት ገፍላችን ተነሳ።

ዛሬ በሸራተን አዲስ ሆቴል ጠዋት ሦስት ሰዓት ተጀምሮ እስከ ምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ድረስ በቀጠለው የውይይት ጉባዬ 28 ጊዜያዊ የዑለማዎች አገዥ ምክር ቤት ተቋቁሟዋል። እንዲሁም 7 ጊዜያዊ አጋዥ ቦርድ አባላት ተመርጠዋል።

ብዙ የመወያያ ሰንዶች፣ ሕጎችደ፣ መተዳዳሪያዎች ደንቦች ቀርበው ተወያይተውባቸው ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።

ከአዳራሽ ሲወጡ...

\\"አልሃምዱሊላሂ ~ #ድምፃችን ተሰማ\\" እያሉ ነበር\\

Via Getu Temesgen
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1