TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ደብረ_ብርሃን_ዩኒቨርሲቲ

ተመራቂዎች በኢትዮጵያ እየታዬ ያለውን የሰላም መደፍረስ እና ዘረኝነት እንዲታገሉ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አሳሰበ፡፡ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለተከታታይ ሶስትና ከዚያ በላይ ዓመታት ያሰለጠናቸውን ከ3 ሺህ በላይ ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በመደበኛ እና በተከታታይ መርሀ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 3 ሺህ 64 ተማሪዎች ማስመረቁ ታውቋል፤ 1 ሺህ 226 የሚሆኑት ደግሞ ሴቶች ናቸው፡፡

የዩኒቨርሲቲው ተወካይ ፕሬዝዳንት ዶክተር ደረጀ አንዳርጌ ተመራቂዎች ያካበቱትን እውቀት ተጠቅመው ሕዝባቸውን እና ሀገራቸውን በታማኝነት እና በቅንነት እንዲያገለግሉ መልዕክት አስተላፈዋል፡፡

በኢትዮጵያ እየታዬ ያለውን የሰላም መደፍረስ እና ዘረኝነት ለመታገልም በቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል፡፡ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮውን ሳይጨምር ከ26 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ማስመረቁ ታውቋል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia