TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የቀድሞዉ የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አማረ አምሳሉን ጨምሮ በ10 የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ላይ ዐቃቤ ሕግ ክስ መስርቷል።

ተከሳሾች፦

1ኛ ተከሳሽ አማረ አምሳሉ፣
2ኛ ተከሳሽ ወልደጊዮርጊስ ወልዱ፣
3ኛ ተከሳሽ ኢሳያስ ዳኘው፣
4ኛ ተከሳሽ አብዱል ሃፊዝ አህመድ፣
5ኛ ተከሳሽ ማስረሻ ጥላሁን፣
6ኛ ተከሳሽ ሰይፈ ኃይለስላሴ፣
7ኛ ተከሳሽ ፀጋየ መኮንን፣
8ኛ ተከሳሽ አይተንፍስ ወርቁ፣
9ኛ ተከሳሽ ጌታሁን ያሲን እንዲሁም
10ኛ ተከሳሽ ሳሙኤል ፈጠነ ሲሆኑ ስልጣንን #ያላግባብ በመገልገል እንዲሁም የመንግስትን ስራ በማያመች አኳኋን በመምራት ከባድ የሙስና ወንጀል ከ259 ሚሊየን ብር በላይ በኢትዮ ቴሌኮም፣ በህዝብና በመንግስት ላይ ጉዳት በማድረስ ወንጀል ተጠርጥረው ዐቃቤ ሕግ በትላንትናው ዕለት ክሱን መስርቷል፡፡

Via የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ
ፎቶ: ፋይል
🗞ቀን ሃምሌ 3/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia