TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
10 ዓመት ?

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ዞን ባምበሲ ወረዳ መንደር 44 ቀበሌ በሁለት #የ8_አመት_ህፃናት ላይ የግብረ-ስጋ ድፍረት (አስገድዶ የመድፈር) ወንጀልን የፈፀመ የ41 አመት ጎልማሳ በ10 አመት ፅኑ እስራት መቀጣቱ ተሰምቷል።

ተከሳሽ አብዱ ወዚር የሚባል ሲሆን ነዋሪነቱ አሶሳ ዞን ባምበሲ ወረዳ መንደር 44 ቀበሌ ነው።

በጥር 3 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ 9 ሰዓት በአካባቢው የማሽላ ሰብል ማሳ ውስጥ በመደበቅና ህፃናቱን " ጥንቅሽ ልስጣችሁ ኑ ብሉ " ብሎ በመጥራት ወደ ውስጥ ካስገባቸው በኋላ ሁለቱንም በሀይል አስሮ የግብረ ስጋ-ድፈረት (አስገድዶ መድፈር) መፈፀሙ ተገልጿል።

በተጨማሪም በህፃናቱ ላይ ያደረሰባቸውን ሁለንተናዊ ጉዳትም ለማንም ትንፍሽ እንዳይሉ አስፈራርቶ እና በገንዘብ አታሎ ከቦታው ይሰወራል።

ፓሊስም ግለሰቡ በቁጥጥር ስር አውሎ ፍርድ ቤት ያቀርበዋል።

የባምበሲ ወረዳ ፍርድ ቤትም ግለሰቡ በ10 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ግለሰቡ ግን " በፍርድ ውሳኔው ላይ ቅር ተሰኝቻለሁ " በማለት ይግባኝ ብሎ ጉዳዩ በአሶሳ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኩል እንዲታይ ይጠይቃል።

የአሶሳ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም " የ10 አመት " ፅኑ እስራት ውሳኔው አስተማሪ ነው በማለት አጽድቆ መዝገቡን ዘግቷል"

Via @TikvahethMagazine
😡1.96K😭265114😢57😱42🙏28👏24🤔24🕊24🥰2