TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጋዜጠኛ ዣማል ካሾግዢ‼️

በሳዑዲ አረቢያዊው ጋዜጠኛ ዣማል ካሾግዢ ግድያ ውስጥ “እጃቸው አለ” ያለቻቸው አሥራ ስምንት ሰዎች ወደ ድንበር ወደማይገድበው የአውሮፓ ሃገሮች የዝውውር ክልል ወደሆነው ሸንገን ቀጣና እንዳይገቡ ጀርመን #እገዳ መጣሏን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ሃይኮ ማስ አስታወቁ።

በርሊን በግለሰቦቹ ላይ እገዳውን ከመጣሏ በፊት ከፈረንሣይ እና ከእንግሊዝ ጋር መመካከሯንም ጀርመናዊው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
ገልፀዋል።

ብራስልስ ላይ ከተሰበሰሰው የአውሮፓ ኅብረት ጉባዔ ጎን ለጎን በተካሄደ መግለጫ ላይ የተናገሩት ማስ “አሁን በራሱ በወንጀሉ ላይና አድራጎቱ እንዲፈፀም ማን እንዳዘዘ መለየትን ጨምሮ ከመልሶቹ ጥያቄዎቹ ይበዛሉ” ብለዋል።

የዣማል ኻሾግዢ ግድያ እንዴት እንደተፈፀመ የሚጠቁመው የተቀረፀ ድምፅ ምን እንደሆነ ሙሉ ማብራሪያ እንደተሰጣቸው ትናንት የተናገሩት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በአድራጎቱ የአመፃና የክፋት መጠን መብዛት ምክንያት ድምፁን እራሱን ማዳመጥ እንደማይፈልጉ ገልፀዋል።

“የሥቃይ ድምፅ ነው፤ አስቀያሚ ድምፅ ነው፤ ሁከትና አመፃ የበዛበት፣ #የጭካሄና የክፋት አድራጎት ነው” ብለዋል።

ምንጭ፦ VOA የአማርኛው አግልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1