" ... ሱዳን እየሄደችበት ያለው መንገድ የተሳሳተ እና የማይጠቅማት በመሆኑ ከድርጊቷ ብትቆጠብ መልካም ነው" - አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የሆኑት አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ፤ ሱዳን ከተሳሳተው መንገዷ እንድትመለስ አሁንም ኢትዮጵያ ትጠይቃለች አሉ።
ሱዳን በተጠናቀቀው አመት የኢትዮጵያን ድንበር አልፋ የተለያዩ ትንኮሳዎችን ማድረጓን ያስታወሱት አምባሳደር ዲና " አሁንም ሱዳን ከተሳሳተው መንገዷ እንድትመለስ ኢትዮጵያ ትጠይቃለች " ብለዋል።
አምባሳደር ዲና ፥ የኢትዮጵያ መንግስት ከሱዳን ጋር ያለውን የድንበር ውዝግብ በትዕግስት መከታተሉን ያነሱ ሲሆን በተጠናቀቀው 2013 ዓ / ም ኢትዮጵያ ከገጠሟት ችግሮች የሱዳን ድንበር ውጥረት አንዱ መሆኑን አስታውቀዋል።
ቃል አቀባዩ ፥ " ችግሩ ባይፈታም ኢትዮጵያ 🇪🇹 ግን ጉዳዩን በበሳል ዲፕሎማሲ እይታ ተከታተለዋለች " ብለዋል። ሱዳን እየሄደችበት ያለው መንገድ የተሳሳተና የማይጠቅማት በመሆኑ ከድርጊቷ ብትቆጠብ መልካም እንደሆነ ተናግዋል፡፡
ከእንደዚህ አይነት ድርጊት በዘለለ ደግሞ #የአፍካውያን_ኩራት በሆነው አየር መንገዳችን ስም ለማጠልሸት የሚደረገውንም ድርጊት ኮንነዋል፡፡
Credit : Ethio FM 107.8
@tikvahethiopia
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የሆኑት አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ፤ ሱዳን ከተሳሳተው መንገዷ እንድትመለስ አሁንም ኢትዮጵያ ትጠይቃለች አሉ።
ሱዳን በተጠናቀቀው አመት የኢትዮጵያን ድንበር አልፋ የተለያዩ ትንኮሳዎችን ማድረጓን ያስታወሱት አምባሳደር ዲና " አሁንም ሱዳን ከተሳሳተው መንገዷ እንድትመለስ ኢትዮጵያ ትጠይቃለች " ብለዋል።
አምባሳደር ዲና ፥ የኢትዮጵያ መንግስት ከሱዳን ጋር ያለውን የድንበር ውዝግብ በትዕግስት መከታተሉን ያነሱ ሲሆን በተጠናቀቀው 2013 ዓ / ም ኢትዮጵያ ከገጠሟት ችግሮች የሱዳን ድንበር ውጥረት አንዱ መሆኑን አስታውቀዋል።
ቃል አቀባዩ ፥ " ችግሩ ባይፈታም ኢትዮጵያ 🇪🇹 ግን ጉዳዩን በበሳል ዲፕሎማሲ እይታ ተከታተለዋለች " ብለዋል። ሱዳን እየሄደችበት ያለው መንገድ የተሳሳተና የማይጠቅማት በመሆኑ ከድርጊቷ ብትቆጠብ መልካም እንደሆነ ተናግዋል፡፡
ከእንደዚህ አይነት ድርጊት በዘለለ ደግሞ #የአፍካውያን_ኩራት በሆነው አየር መንገዳችን ስም ለማጠልሸት የሚደረገውንም ድርጊት ኮንነዋል፡፡
Credit : Ethio FM 107.8
@tikvahethiopia