TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ችሎት

በምእራብ አርሲ ሄቨን ወረዳ 177 ችግኞችን #የነቀለው ግለሰብ በስድስት አመት ጽኑ እስራት ተቀጣ፡፡ በምእራብ አርሲ የሙኔሳ ወረዳ ፍርድ ቤት ሃምሌ 12፣ 2011 በዋለው ችሎት ሄቨን አርሲ ወረዳ ደጋጋ ቀበሌ 177 ችግኞችን በመንቀል የተጠረጠውን ግለሰብ ፋይል ተመልክቷል፡፡ ግራ ቀኙን የተመለከተው ፍርድ ቤቱ የወረዳው ነዋሪ የሆነው ትቤሶ ያለቱ ሃምሌ 9፣ 2011 ከቀኑ ስድስት ሰዓት አካባቢ በሙኒሳ ዲስትሪክት የመንግስት ደን ውስጥ በዚህ ክረምት ከተተከሉችግኞች መካከል 177 ችግኞችን በመቀል በቀረበበት ክስ ጥፋተኛ ብሎታል፡፡ በዚህም በተከሳሹ ላይ የስድስት ዓመት ጽኑ እስራት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ችግኞቹ 3 ሺህ 640 ብር ግምት እንዳላቸውም ነው የተገለጸው

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia