TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የትግራይ_ህዝብ_ፍቅር_ነው!

"ወደ ትግራይ እንዳትሄድ ብለው አስጠንቅቀውኝ ነበር! የመጣነው ከአዳማ፣ ኦሮሚያ ነው። ልጆቻችን ለማስመረቅ ወደ መቐለ እንሄዳለን ብለን ስንናገር #ይቅርባችሁ ተብለናል። እንሄዳለን ብለን ስንወስንም በሉ አፋን ኦሮሞ እንዳትናገሩ ብለው መክረው ስለ ላኩን አሁን ግን የቴሌቪኑ የስርጭት ቋንቋ አማርኛ ቢሆንም ደስታዬ እና መልእክቴን በአፋን ኦሮሞ ነው ማስተላልፈው!" ብለው በኣፋን ኦሮሞ ደስታቸውን መልዕክታቸውን ተናገሩ። (ከትግራይ ህዝብ ጋር 'በ በሬ ወለደ ውሸታቸው ሊለያዩን የሚያስቡ ሰዎች ጤነኛ ናቸውን?) በማለት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በአፋን ኦሮሞ ሐሳባቸውን ገለፁ።

የትግራይ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛም ጎበዝ ነበር እንደ እሳቸው በአፋን ኦሮሞ ጥያቄውን አስከተለ (አንድ ቋንቋ የሚናገር አንድ ሰው ነው:ሁለት የሚናገር ሁለት ሰው ነው ይባል የለ?) ጋዜጠኛው ብዙ ሰው ነበረ፡፡ እንግዳውም ቀጥለው... በአማርኛ ቋንቋ የትግራይ ህዝብ በሄዱበት መስጊድ፣ ምግብ ቤትና መኝታ ቤት በታላቅ ክብር እንዳስተናገዷቸው ገልፀው አመሰገኑ፡፡"

ፍቅር፤ ሰላም፤ አንድነት!
@tsegabwolde @tikvahethiopia