TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የቅዱስ_ገብርኤል_ንግስ_በዓል_ቁልቢ

ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል ንግስ በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር በድምቀት ትላንት ተከብሯል።

በዓሉ ያለፀጥታ ችግር ይጠናቀቅ ዘንድ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ፣ የሀረር እና ኦሮሚያ ልዩ ኃይሎች ፣ የፌዴራል ፖሊስ እንዲሁም የቁልቢ ከተማ ፖሊስ በቅንጅት መስራታቸው ተገልጿል።

በዓሉ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ምንም የትራፊክ አደጋ አልተከሰተም።

በበዓሉ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስና ሌሎችም ብፁዓነ ሊቃነ ጳጳሳት ተገኝተው ነበር።

*
*
በስርቆት ወንጀል የተከሰሱ 4 ግለሰቦች ፦

በቁልቢ ገብርኤል ንግስ በዓል በስርቆት ወንጀል የተከሰሱ አራት ግለሰቦች በእስራት እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል።

ግለሰቦቹ በንግስ በዓሉ ሞባይል ስልክና ሌሎች ቁሳቁሶችን ሲሰርቁ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።

አራቱ ግለሰቦች እስከ አንድ አመት ከስምንት ወር በሚደርስ እስራት ነው የተቀጡት።

#DirePolice #ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia