TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ስውር እስር ቤቶች በአዲስ አበባ‼️

በአዲስ አበባ ከሰባት(7) በላይ የሚደርሱ #የስውር እስር ቤቶች እንዳሉ ተሰምቷል። በሌሎችም የክልል ከተሞች የድብቅ ማሰሪያ ቤት እንዳሉ አቃቤ ህግ ተናግሯል፡፡

ወንጀል ሰርተዋል ተብለው የሰብዓዊ መብት የተጣሰባቸው ሰዎች #በአምቡላንስ ተጭነው እንደሚያዙ አይናቸውም ታስሮ በስውር ማረሚያ ቤት በድብደባ እንዲያምኑ እንደተደረገ በምርመራ መደረሱን የፌዴራል አቃቤ ህግ ተናግሯል፡፡

ይህም ከህገ መንግስቱ ጋር ሙሉ ለሙሉ የተጣረሰ እንደሆነ አቃቤ ህግ #ብርሃኑ_ፀጋዬ ተናግረዋል፡፡

የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ተገደው እንዲወጡ ይህንንም ካላደረጉ ከፍተኛ ድብደባ እንደሚፈፀምባቸው ተሰምቷል፤ መሳሪያ እላያቸው ላይ ተተኩሷል፡፡

በሚስጥራዊ እስር ቤት የቆዩ ሰዎችም የተለያዩ ሰብዓዊ መብት #ጥሰት እና #የማሰቃየት ስራ ተደርጓል።

አካልን በኤሌክትሪክ ማንዘር የብልት ቆዳን በፒንሳ መሳብ፣ እስክሪቢቶ አፍንጫ ውስጥ መክተት፣ ጫካ ውስጥ ከአውሬ ጋር እርቃን ማሳደር፣ ምግብ መከልከል እና ሌሎችም የሰው ልጅ ለራሱ ዝርያ ማድረግ የማይገባውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት መደረጉን የጠቅላይ አቃቤ ህግ በአምስት ወር የምርመራ ጊዜ አረጋግጫለው ብሏል፡፡

በዚህም ምክንያት ሴቶች እንደተደፈሩ በወንዶች ላይም የግብረሰዶም ጥቃት እንደተፈፀመ ጨለማ ውስጥም የቆዩ አይናቸው እንደጠፋ የተለያዩ መረጃዎች አስረድተዋል፡፡

ተጠርጥረዋል የተባሉት ኢትዮጵያውያን የራሳቸው ያልሆኑ የጦር መሳሪያዎች እና ሰነዶች ላይ በግድ እንዲፈርሙ በዚህ ሂደትም የተገደሉ እና የተሰወሩ መኖራቸው ታውቋል።

በዚህ መሰረትም ይህንን በደል የፈፀሙ ከፍተኛ የደህንነት መስሪያ ቤት ኃላፊዎች ለምርመራ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia