TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

' ቲክቶክ ' አሜሪካ ውስጥ ከታገድኩኝ " የ170 ሚሊዮን አሜሪካውያን የመናገርና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ይረገጣል " አለ።

ይህን ያለው የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት መተግበሪያው ከቻይና ካልተፋታ እንዲታገድ ረቂቅ ህግ ካጸደቁ በኃላ ነው።

የ 'ቲክቶክ' ቃል አቀባይ መተገበሪያው እንዲታገድ የሚለውን ረቂቅ ህግ አውግዘዋል።

" ከታገደ ፦
- የ170 ሚሊዮን አሜሪካውያንን የመናገር መብት ይረግጣል፣
- 7 ሚሊዮን ንግዶች እንዲጠፉ ይሆናል፣
- ለአሜሪካ ኢኮኖሚ በዓመት የሚገባውን 24 ቢሊዮን ዶላር ያሳጣል " ብለዋል።

አክለው ፤ " ባይትዳንስ የቻይና ወይም የሌላ አገር ወኪል አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።  " የቻይና ኩባንያ እንዳልሆነም በተደጋጋሚ ተናግረናል " ሲሉ አክለዋል።

ጉዳዩን የሚከታተሉ አካላት ግን ' ቲክቶክ ' ከቻይና ተፋቶ ድርሻው ለአሜሪካ ሰዎች ካልተሸጠ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ #የመታገዱ ነገር አይቀሬ ነው ብለዋል።

ትላንት የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ' ቲክቶክ ' በመላው ሀገሪቱ እንዲታገድ የሚያደርግ ረቂቅ ህግ አጽድቋል።

@tikvahethiopia