TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ሰማያዊ፣ ኢራፓ፣ መኢአድና ሌሎች ፓርቲዎችን ያሰባሰበው “የብሔራዊ መግባባትና ዕርቀ ሠላም ኮሚቴ” በአዲስ አበባ ፓርቲዎችን
ለምክክር ጠርቷል፡፡ ከአስተባባሪዎቹ አንዱ የሆኑት መላኩ መሰለ “በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚታየው ችግር በተናጠል ወይም በቡድን መፍትሔ ከሚሰጥበት አቅም በላይ በመሆኑ ተሰባስቦ መፍትሔ መፈለግ ይገባል” ነው ያሉት፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሁሉም የፖለቲካ ድርጅቶች የሠላም ጥሪ ቢያደርግም በየቦታው የሚታዩ ግጭቶች አስነዋሪና #ዘግናኝ ባሕሪያትን እየያዙ በመምጣታቸው ስብሰባው በአስቸኳይ መጠራቱን አስተባባሪዎቹ ጠቁመዋል፡፡

©ዋዜማ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
FM_20181229_224505.ogg
8.5 MB
አዲስ አበባ‼️

የፍቅረኛውን #ብልት በክር የሰፋው ኢትዮጵያዊ...እጅግ በጣም ለመስማት የሚከብድ #ዘግናኝ ድርጊት አዲስ አበባ አስተናገደች!!

ምንጭ፦ ኢትዮፒካሊንክ የራድዮ ፕሮግራም(FM 98.1)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር አብይ ሀዘናቸውን ገልፁ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር #ዐቢይ_አህመድ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ በሰላማዊ ዜጎች ላይ በተፈጸመው ጥቃት መንግሥት የተሰማውን ሀዘን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቃቱ በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመ #ዘግናኝ ድርጊት ሲሉ ኮንነውታል። ለተጎጂ ቤተሰቦችና በሀዘን ላይ ለሚገኙት መላው ኬንያውያን የተሰማቸውን ልባዊ ሀዘን ገልጸዋል። ትናንት ናይሮቢ ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት 14 ሰዎች መገደላቸውን የኬንያው ፕሬዚዳንት #ኡሁሩ_ኬንያታ ዛሬ መግለጻቸው ይታወሳል።

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia