" አኲርፈው የተለዩትን በጠባይ ወደ እኛ እናምጣቸው ፤ እኛም ኲርፊያን ከሚያስከትል ድርጊት እንራቅ " - ቅዱስነታቸው
የጥቅምት ወር 2016 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ተከፈተ።
ምልዓተ ጉባኤው የተከፈተው ፥ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር ነው።
ቅዱስነታቸው ምን አሉ ?
ቅዱስነታቸው ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር ወቅት ፤ ቤተክርስቲያኗ አሁን ለጀመረችውና ለወደፊትም ለምትጀምራቸው የመልካም አስተዳደርና የልማት ስራዎች ዋስትና እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
" የስራዎቻችን ዋስትና በሀገርና በቤተክርስቲያን ፍጹም የሆነ ሰላምና አንድነት መኖር ነው " ብለዋል።
የጠማንን ሰላምና አንድነት መልሶ ለማምጣት የቤተክርስቲያን ኃይል የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወስድ ገልጸዋል።
ሆኖም የቤተክርስቲያን የሰላም ጉዞ ከማንኛውም #ወገንተኝነት_በጸዳ፣ ማእከሉና ዓላማው የሀገርና የቤተክርስቲያንን አንድነት ብቻ መሠረት ያደረገ መሆን እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
ከዚህ አንጻርም በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በቤተክርስቲያንም እንከን የለሽ አንድነት እንዲረጋገጥ በብርቱ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።
" አኲርፈው የተለዩትን በጠባይ ወደ እኛ እናምጣቸው " ያሉት ቅዱስነታቸው " እኛም ኲርፊያን ከሚያስከትል ድርጊት እንራቅ። በአንድነት፣ በእኩልነትና በጋራ ሆነን ታላቋን ቤተክርስቲያን እንሰብስብ፣ እናገልግል፣ እንምራ፣ እንጠብቅ፡፡ ለዚህም ሙሉ ዝግጅት እናድርግ። " ብለዋል።
ቅዱስነታቸው ፤ " የዕለት ተዕለት ስራችን የቤተክርስቲያንን ጭንቀት የሚያቃልል ይሁን " ያሉ ሲሆን " ይህ ከሆነ ቤተክርስቲያንን ያለ ምንም ጥርጥር በዕድገት ጐዳና ወደ ፊት እናሻግራለን " ሲሉ ገልጸዋል።
የታላቋን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን መርምሮ ገምግሞና አጥንቶ ችግር ፈቺ ውሳኔን የመስጠት ኃላፊነት ያለው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተከፈተ መሆኑንም ቅዱስነታቸው በቤተክርቲያን ስም አብስረዋል።
(የቅዱስነታቸው ሙሉ ንግግር ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የጥቅምት ወር 2016 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ተከፈተ።
ምልዓተ ጉባኤው የተከፈተው ፥ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር ነው።
ቅዱስነታቸው ምን አሉ ?
ቅዱስነታቸው ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር ወቅት ፤ ቤተክርስቲያኗ አሁን ለጀመረችውና ለወደፊትም ለምትጀምራቸው የመልካም አስተዳደርና የልማት ስራዎች ዋስትና እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
" የስራዎቻችን ዋስትና በሀገርና በቤተክርስቲያን ፍጹም የሆነ ሰላምና አንድነት መኖር ነው " ብለዋል።
የጠማንን ሰላምና አንድነት መልሶ ለማምጣት የቤተክርስቲያን ኃይል የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወስድ ገልጸዋል።
ሆኖም የቤተክርስቲያን የሰላም ጉዞ ከማንኛውም #ወገንተኝነት_በጸዳ፣ ማእከሉና ዓላማው የሀገርና የቤተክርስቲያንን አንድነት ብቻ መሠረት ያደረገ መሆን እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
ከዚህ አንጻርም በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በቤተክርስቲያንም እንከን የለሽ አንድነት እንዲረጋገጥ በብርቱ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።
" አኲርፈው የተለዩትን በጠባይ ወደ እኛ እናምጣቸው " ያሉት ቅዱስነታቸው " እኛም ኲርፊያን ከሚያስከትል ድርጊት እንራቅ። በአንድነት፣ በእኩልነትና በጋራ ሆነን ታላቋን ቤተክርስቲያን እንሰብስብ፣ እናገልግል፣ እንምራ፣ እንጠብቅ፡፡ ለዚህም ሙሉ ዝግጅት እናድርግ። " ብለዋል።
ቅዱስነታቸው ፤ " የዕለት ተዕለት ስራችን የቤተክርስቲያንን ጭንቀት የሚያቃልል ይሁን " ያሉ ሲሆን " ይህ ከሆነ ቤተክርስቲያንን ያለ ምንም ጥርጥር በዕድገት ጐዳና ወደ ፊት እናሻግራለን " ሲሉ ገልጸዋል።
የታላቋን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን መርምሮ ገምግሞና አጥንቶ ችግር ፈቺ ውሳኔን የመስጠት ኃላፊነት ያለው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተከፈተ መሆኑንም ቅዱስነታቸው በቤተክርቲያን ስም አብስረዋል።
(የቅዱስነታቸው ሙሉ ንግግር ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
❤1.6K🙏178🕊71😡63😭27🥰22😢11😱8