TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ውሎው ችግር ባለባቸው እና አስፈላጊ በሆኑባቸው አህጉረ ስብከት 9 አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት #እንዲሾሙ ውሳኔ ማሳለፉን የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ዘግቧል። @tikvahethiopia
#Update

" የሹመቱ ቀን #ወደፊት ይገለፃል " - ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር)

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን በተመለከተ አጭር መግለጫ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

- የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ #በሰላም እና ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቋል።

- ዛሬ የመጨረሻው አጀንዳ ላይ ብዙ ውይይት ተካሂዷል።

- በመጨረሻ ሁሉም አባቶች ተወያይተው ቤተክርስቲያንን የሚጠቅመው ምንድነው ? የሚለው ላይ በመምከር ዛሬ ውሳኔ ተላልፏል።

- የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት እንዲካሄድ ተወስኗል። የመጀመሪያው ችግር ያለባቸው ሀገረ ስብከት የሚል ሲሆን አሁን 7 አባላት ያሉት ኮሚቴ ተቋቁሟል እነሱ በሚያቀርቡት ጥናት ሹመት ይካሄዳል። የሹመቱ ቀን #ወደፊት ይገለፃል። ዋናው ነገር ለቤተክርስቲያን የሚጠቅመው የትኛው ነው ? የሚለውን የጉባኤው አባላት በሙሉ ተስማምቶ ፣ በአንድ ልብ፣ በአንድ ሃሳብ፣ በመነጋገር ውሳኔ ተላልፏል።

- ረቡዕ የማጠቃላይ መግለጫ በቅዱስ ፓትርያርኩ ይሰጣል።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) ፦

" ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን፤ ምዕመናን በሙሉ ተጨንቃችኃል፤ አንዳንድ ጊዜ እውነት ነው ሌላ ጊዜ ወሬም ብዙ ይበዛል በዚህ ሚዲያ በበዛበት ዘመን በጣም ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን ፤ በእውነት እግዚአብሔርን እናመሰግናለን ግሩም የሆነ የትምህርት ጊዜ፣ ግሩም የሆነ የውይይት ጊዜ ፣ ቤተክርስቲያን ለይተን የምትፈልገው ምንድነው የሚለውን የተወያየንበት ጊዜ ነው ፤ እግዚአብሔርን እናመሰግናለን !! "

@tikvahethiopia
👍3.31K352👎273🕊259🙏195😢42🥰29😱26
TIKVAH-ETHIOPIA
ተጀመረ ! በከፍተኛ ጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የ10,000 ሜትር የወንዶች ፍፃሜ ውድድር ተጀምሯል። ሀገራችን ፦ - በአትሌት በሪሁ አረጋዊ - በአትሌት ሰለሞን ባረጋ - በአትሌት ይስማው ድሉ ተወክላለች። ውድድሩን በብሔራዊ ቴሌቪዥን መዝናኛ ቻናል እንዲሁም በDSTV 226 ላይ መመልከት ይቻላል። ድል ለሀገራችን ! ድል ለአትሌቶቻችን ! @tikvahethiopia
#Update

ውድድሩ ከጀመረ አንስቶ የኬንያ እና የዩጋንዳ አትሌቶች ከፊት መስመር ሆነው ዙሩን እያከረሩት ነበር።

ለተወሰነ ዙር በሪሁ አራጋዊ ወደፊት መጥቶ ዙሩን ሲመራ የነበረ ሲሆን አሁን መሪነቱን ኬንያውን ተረክበዋል።

ሌላኛው የሀገራችን ልጅ ይስማው ድሉ ከመሪዎቹ በቅርብ ርቀት ላይ ነው የሚገኘው።

ሰለሞን ባረጋ መጨረሻ ላይ የነበረ ሊሆንም አሁን ላይ #ወደፊት እየመጣ ነው።

አንድ ዩጋንዳዊ አትሌት አቋርጦ ወጥቷል።

አሁን 10 ዙር ይቀራል።

ድል ለሀገራችን !!

@tikvahethiopia
👍49191🙏44👏35👎28🕊15😱14🥰11
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሀዋሳ " ... በነዳጅ እጥረት ስራችንን መስራት አልቻልንም። ተሰልፈን ነው የምንውለው " - አሽከርካሪዎች " ባለፉት ሁለት ሳምንታት ከጅቡቲ የሚመጣው ነዳጅ መዘግየቱን ተከትሎ ነው ችግር የተፈጠረው " - የከተማው ገበያ ልማት በሀዋሳ ከተማ የነበረዉ ከፍተኛ የነዳጅ እጥረትና ሰልፍ ተስተካከለ ተብሎ ጥቂት ጊዜያት ሳይቆይ ድንገት ችግሩ ማገርሸቱን ተከትሎ መጨረሻ የሌላቸው የሚመስሉ ሰልፎች በየማደያዉ…
#ሀዋሳ

በሀዋሳ ከተማ የህዝብ ትንራንስፖርት አገልግሎት (ታክሲ) የሚሰጡ አሽከርካሪዎች ፤ " የነዳጅ ጉዳይ ስቃያችንን አበላን ፤ የመፍትሄ ያለህ !! " ሲሉ ድምፃቸውን አሰምተዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የታክሲ አገልግሎት ሰጪ አሽከርካሪዎች ፤ "ሰርተን ከምንገባበት ለነዳጅ ሰልፍ ቆመን የምንውለበት እየበለጠ ነው " ብለዋል።

የነዳጅ ችግሩ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ዛሬም ድረስ የቀጠለ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።

የቤተሰብ አስተዳዳሪ እንደሆኑም በመግለፅ "
ካልሰራን ልጆቻን ምን ይብሉ ? ፤ እኛስ ምን በልተን እንደር ? ይህ ጉዳይ መፍትሄ ይፈልጋል " ብለዋል።

ከሳምንታት በፊት በዚሁ በሀዋሳ ከተማ ያሉ አሽከርካሪዎች ፤ " በረዣዥም ሰልፍችና በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ስራችን በአግባቡ መስራት አልቻልንም " በሚል ምሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተው ነበር።

አሽከርካሪዎች ፤ ሁሉም ማደያዎች በአግባቡ አለመስራትና ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ መኪኖች ለነዳጅ ሰልፍ ተገፍተዉ ከመግባት ባለፈ ከፍተኛ መጠን ያለዉ ሳልቫቲዮ ገጥመዉ መምጣታቸው ቀኑን ሙሉ ተሰልፈዉ እንኳን መቅዳት እንዳይችሉ ምክኒያት እንደሆነባቸው ገልጸው ነበር።

በወቅቱ እየተነሳ ላለው ቅሬታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የሰጡት የሀዋሳ ከተማ ገበያ ልማት ቢሮ የስነልኬት ባለሙያው አቶ ሀብታሙ መኮንን ፤ ችግሩ መኖሩን አምነው ፤ ከጅቡቲ የሚመጣው ነዳጅ መዘግየቱን ተከትሎ የተፈጠረው ክፍተት ለችግሩ ምክንያት እንደሆነ ገልጸው ነበር።

ችግሩም " #ወደፊት_ይቀረፋል " የሚል ተስፋ እንዳላቸዉ ማመልከታቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
😢24786🙏30😭19🕊17😱13😡13🥰9👏7
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር " መደበኛ ያልሆነን የጎዳና ላይ ንግድ ስርዓት ለማስያዝ ይረዳል " ያለውን ደንብ አውጥቷል።

የደንቡን መውጣት ተከትሎ ንግዱ የሚካሄድበት ሰዓት በ5 ፈረቃ ተከፋፍሎ ይፋ ሆኗል።

በዚሁ መሰረት ፦

➡️ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 1:00 ሰዓት የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የአልባሳት እና መጫሚያዎች ንግድ እንዲካሄድ፤

➡️ ከንጋቱ 1:00 ሰአት እስከ ረፋዱ 3:00 ሰዓት እንደ ብስኩት ፣ ሻይ ፣ ቡና ፣ የታሸገ ውሃ እና ለስላሳ መጠጦች ያሉ እና ለቁርስ የሚሆኑ ቀላል ያሉ ምግቦች ንግድ እንዲካሄድ ፤ የጫማ ፅዳት ወይም ሊስትሮ አገልግሎት በዚሁ ሰዓት እንዲካሄድ፤

➡️ ከረፋዱ 3:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 6:00 የመፅሃፍት ፣ መፅሄቶች እና ጋዜጦች ንግድ እንዲካሄድ፤

➡️ ከቀኑ 6:00 ሰዓት እስከ 8:00 ሰዓት ቀላል ምግቦች በመባል የሚታወቁት እንደ ኬክ ፤ ብስኩት ፤ ሻይ ፤ ቡና ፤ የታሸገ ውሃና ለስላሳ መጠጦች ንግድ እንዲካሄድ፤

➡️ ከአመሻሽ 11:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ተኩል የተጠበሱ ምግቦች ፣ ጁስ ፣ ብስኩት ፣ ኬክ ፣ ሻይ ፣ ቡና ፣ የታሸገ ውሃ እና ለስላሳ መጠጦች እንዲሁም አልባሳት እና መጫሚያዎች ፣ ቀላል የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎች ፣ የውበት መጠበቂያ ኮስሞቲኮስች ንግድ እንዲካሄድ የከተማ አስተዳደሩ መርሃ ግብር አውጥቷል።

ንግዱ የሚካሄድባቸው ቦታዎች
#ወደፊት እንደሚለዩና ይፋ እንደሚደረጉ የከተማ አስተዳደሩ አሳውቋል።

መደበኛ ያልሆነ የጎዳና ላይ ንግድ " ኮንትሮባድን ያበረታታል፤ ለትራፊክ መጨናነቅ እና አደጋም መንስኤ ይሆናል እንዲሁም በህጋዊ ንግዱ ላይ ተፅዕኖ ያሳድራል " በሚል በከተማው አስታዳደር ቁጥጥር እንዲደረግበት ሲሞከር እንደነበር ይታወሳል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።

@tikvahethiopia
😡1.16K484🤔162👏143😭80🙏75💔29🕊28😱21🥰13😢9