TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኩሪፍቱ በሰመራ🔝

አፍሮ ፅዮን ኮንስትራክሽን ኩባንያ በአፋር ክልል ርዕሰ ከተማ #ሰመራ በኩሪፍቱ ሪዞርት ሥር የሚተዳደረውን ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ግንባታ 90 በመቶ በማጠናቀቅ ሥራ አስጀምሯል፡፡

#ኩሪፍቱ_ሪዞርት የሚል መጠሪያ የተሰጠው ይህ ሆቴል ቅዳሜ የካቲት 9 ቀን 2011 ዓ.ም. የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ #አወል_አርባ በተገኙበት የተመረቀ ሲሆን፣ የሆቴሉ ሥራ መጀመር ለክልሉ የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሏል፡፡

148 የመኝታ ክፍሎች ያሉትና ሌሎች ደረጃቸውን የጠበቁ የሆቴል አገልግሎቶችን ያካተተው ሆቴል፣ እስካሁን 500 ሚሊዮን ብር እንደወጣበት ሲገለጽ፣ ለቀሪ ሥራዎች ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚጠይቅ ተጠቁሟል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia