TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በትግራይ 10 ሺ ያህል ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና አልወሰዱም።

በትግራይ ክልል የ2012 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ የነበሩ እና ለፈተና መቀመጥ ያልቻሉ 10,000 ያህል ተማሪዎች ከሁለት ወር በኋላ ይፈተናሉ ተብሏል።

በትግራይ ክልል የ2012 ተፈታኝ የሆኑ ከ12,000 በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንዲቀመጡ ቢጠበቅም የተፈተኑትን ግን 2,130 ብቻ መሆናቸውን የሃገር አቀፍ ትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ገልፀዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ ፥ "መፈተን ከነበረባቸው ከ12,000 በላይ ተማሪዎች በክልሉ ባለው የሰላም ችግር ምክንያት የተፈተኑት 2,130 ብቻ በመሆናቸው ቀሪዎቹ 10,000 ያህል ተፈታኞች #ከ2013_ተፈታኞች ጋር እንዲፈተኑ ተወስኗል" ብለዋል።

የ2013 ዓ.ም ፈተና ከሁለት ወር በኋላ ይሰጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 የሃገር አቀፍ ትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia