TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አምነስቲ ኢንተርናሽናል⬆️

ከትላንት በስቲያ የታሰሩት ጠበቃ #ሄኖክ_አክሊሉና አቶ #ሚካኤል_መላከ ያለ ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች አምነስቲ ኢንተርናሽናል ጠየቀ።

ፖሊስ በምርመራ ጊዜ መጠየቂያ መዝገብ ላይ ለክሱ መነሻ አድርጎ ያቀረበው የመደራጀት ምክንያት “መብት” እንጂ “ወንጀል” አይደለም ሲሉ የአምነስቲ የአፍሪካ ቀንድ ተመራማሪ አቶ ፍሰሃ ተክሌ ለቪኦኤ ገልፀዋል።

ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት አቅርቦ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቆባቸው የነበረ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ሰባት ቀን ፈቅዷል።

ጠበቃ አለልኝ ምሕረቱ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ #ከፍልስጥዔም ኤምባሲ ጋር ግንኙነት ያደርጋሉ መባሉ እንዳሣዘናቸው ተናግረዋል።

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia