TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኢትዮጵያውያኑ ከከፋፋይ ሀሳቦች ይልቅ በአንድነት ላይ እንዲያተኩሩ ተጠየቁ!

በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍፁም አረጋ #በዴንቨር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ትናንት አወያይተዋል። በውይይቱም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በመተባበር ለሀገራቸው የሚያደርጉትን ድጋፍ እንዲያጠናክሩ አምባሳደሩ ጠይቀዋል።

#ጥላቻ እና #ከፋፋይ ሀሳቦችን በመተው ወደ አንድነትና የሚያስማሙ ሀሳቦች ላይ እንዲያተኩሩም ነው መልዕክት የተላለፈው። ለዚህም በአንድነት መሥራት እንደሚገባቸው አምባሳደር ፍፁም ጠይቀዋል። #በዴንቨር የሚኖሩ የዳያስፖራ ማኅበረሰብ አባላትም ኢትዮጵያዊነትን መሠረት ያደረገ ውይይት መዘጋጀቱ ተገቢ መሆኑን መናገራቸውን በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያሳያል።

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia