TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ቬንዙዌላ ድንበሯን ዘጋች‼️

የቬንዙዌላ ፕሬዘዳንት #ኒኮላስ_ማዱሮ #በሰብዓዊነት ስም በተቃዋሚ ፓርቲዎች አማካኝነት ከአሜሪካ የሚደረገውን እርዳታ ለማስቆም አገራቸው #ከብራዚል ጋር የሚያዋስናትን ድንበር መዝጋቷን አስታወቁ፡፡

በዚህ ምክንያትም በርካታ ተሽከርካሪዎች በሁለቱ አገራት ድንበር ላይ ቆመው እንዳሉም ተገልጿል።

ፕሬዘዳንቱ በአገራቸው ከመንግስት አቅም በላይ የሆነ ሰብዓዊ ቀውስ እንደሌለና ምንም አይነት የእርዳታ ጥሪም እንዳልተደረገ ገልፀዋል፡፡

በአገሪቱ በተፈጠረው #አለመረጋጋት አጣብቂኝ ውስጥ የሚገኘው ግራ ዘመሙ መሪ #ማዱሮ በአገሪቱ የቴሌቭዥን ጣቢያ ወጥተው እንደገለፁት የተቃዋሚ መሪዎች በሰብዓዊ እርዳታ ስም ከአሜሪካና ሌሎች አጋሮቿ የሚላከውን ለማስቆም የኮሎንቢያ ድንበርንም ጨምረው እንደሚዘጉ ገልፀዋል፡፡

ይህን ተከትሎም የተቃዋሚ ፓርቲ መሪው ጁዓን ገይዱ በበርካታ አውቶቡሶችና ሌሎች ተሽከርካሪዎች ታጅቦ ከቬንዙዌላ ዋና ከተማ ካራካስ ወደ #ኮሎንቢያ ድንበር ማቅናታቸው ተገልጿል፡፡

በቅርቡ የተካሄደውን ምርጫ ተከትሎ በአገሪቱ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት መፈጠሩ ይታወሳል፡፡

ምንጭ፡-ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia