TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ኢመርሰን ምናንጋግዋ የአገሪቱን የኢነርጂ ሚኒስትር በአገሪቱ የተባባሰውን #የመብራት_መጥፋት ችግር ተከትሎ ከኃላፊነት ማንሳታቸው ተነግሯል። ከሀላፊነታቸው የተነሱት የዚምባብዌ የኢነርጂል ሚኒስትር ጆራም ጉምቦ በትራንስፖርትና መሰረተ-ልማት ምክትል ሚኒስትር ፎርቹን ቻዚ ተተክተዋል፡፡ የቀድሞው የዚምባብዌ ኢነርጂ ሚኒስትር ከኃላፊነታቸው የተነሱት ከ2016 ወዲህ ባልታየ ሁኔታ በየዕለቱ እና በመላ አገሪቱ መብራት ጠፍቶ ለሰዓታት እንደሚቆይ ተቋማቸው ማስታወቁን ተከትሎ ነው፡፡ መንግስታዊው የአገልግሎት ሰጪ ተቋም ከትናንት በስቲያ በሰጠው መግለጫ በየዕለቱ ከ5 እስከ 8 ለሚደርሱ ሰዓታት በመላ አገሪቱ መብራት እንደማይኖር አስታውቆ ነበር፡፡ ተቋሙ ይህን ያለው የአገሪቱ ትልቁ ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ እና በድንጋይ #ከሰል የሚሰሩት አሮጌ ጄነሬተሮች የሚያመርቱት የኃይል መጠን መቀነሱን በመንስኤነት ጠቅሶ ነው፡፡

ምንጭ፡- ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia