TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና⬆️የኬንያ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ማህበር *በኢትዮጵያ አየር ተቆጣጣሪዎች እየተካሄደ ያለው አድማ የአየር- ለአየር የአውሮፕላን #ግጭት ሊፈጥር በሚችል ደረጃ ችግር እየፈጠረ መሆኑን አስታውቀው በኢትዮጵያ ያሉት አካላት ሁኔታው ከፍተኛ አደጋ #ከመፍጠሩ በፊት #መላ እንዲበጁለት ጠይቋል።

ማህበሩ እንዳወጣው ደብዳቤ ከሆነ በአብዛኛው በጡረታ በተሰናበቱ አየር ተቆጣጣሪዎች በአሁን ሰአት እየተመራ ያለው የኢትዮጵያ አየር ክልል አሳሳቢ ነው ብሎ እንደምሳሌ አንድ በቅርብ በተከሰተ አጋጣሚ በአንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ሌላ አየር መንገድ ንብረት በሆነ አውሮፕላን መካከል ችግር ተፈጥሮ እንደነበር ጠቅሷል። በዚህ አጋጣሚም አውሮፕላኖቹ የTCAS (የአየር ለአየር ግጭት መከላከያ) ሲስተማቸውን ለማብራት ተገደው ነበር ብሏል።

የኢትዮጵያ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ከክፍያ፣ ጥቅማጥቅም እና የስራ ቦታ ሁኔታ ጋር ከሰኞ ጀምሮ አድማ ላይ መሆናቸው ይታወቃል።

ደብዳቤ ©Emmanuel Igunza
ዜና ዝግጅት© ኤልያስ መሰረት(AP)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1