TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተን ለማደር ተቸግረናል " - ነዋሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ከጤፍ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተው ለማደር መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። ለሪፖርተር ጋዜጣ ቃላቸውን የሰጡ የከተማው ነዋሪዎች ፤ ሰሞኑን የአንድ እንጀራ ዋጋ ቀደም ሲል ከነበረበት 17 ብር ወደ 22 እና 24 ብር ከፍ በማለቱ፣ ገዝተው ለመጠቀም ተቸግረዋል፡፡ እንጀራን…
የዳቦ እና እንጀራ ዋጋ ስንት ገባ ?
በአዲስ አበባ ከተማ አካባቢዎች (የመኖሪያ መንደሮች) የአንድ ትንሹ ዳቦ ዋጋ ከወራት በፊት ከነበረበት 4 እና 5 ብር አሁን ላይ 9 -10 ብር መድረሱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል።
የዳቦ ዋጋ ባለፈው ዓመት 5 ብር በገባበት ወቅት ብዙ ሲባል የነበረ ሲሆን በተወሰኑ ወራት ልዩነት እጥፍ በሚያስብል ደረጃ እንደጨመረ አመልክተዋል።
ሁሉም ነገር የአንድ ሰሞን የማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ይሆንና መፍትሄ ሳይሰጠው በዛው ይቀጥላል ፤ የኑሮው ጫና እጅግ እየከበደ ነው ብለዋል።
መፍትሄው ግራ የሚያጋባ ነው ያሉት አስተያየታቸውን የላኩ የቤተሰባችን አባላት ፤ የአንድ ዳቦ ዋጋ ቀስበቀስ እየጨመረ መጥቶ ወደ 10 ብር ተጠግቷል ፤ ከዚህ ቀደም ጨመረ ተብሎ ለተነሳው ሮሮ መፍትሄ ሳይሰጥ #እንድንለማመደው ተደረገ አሁንስ እንዲሁ ይቀጥላል ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ከሰሞኑን ሪፖርተር ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ከጤፍ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተው ለማደር መቸገራቸውን መገለፃቸው ይታወሳል።
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ ሰሞኑን የአንድ እንጀራ ዋጋ ቀደም ሲል ከነበረበት 17 ብር ወደ 22 እና 24 ብር ከፍ በማለቱ፣ ገዝተው ለመጠቀም መቸገራቸውን ገልጸው እንደነበር አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ አካባቢዎች (የመኖሪያ መንደሮች) የአንድ ትንሹ ዳቦ ዋጋ ከወራት በፊት ከነበረበት 4 እና 5 ብር አሁን ላይ 9 -10 ብር መድረሱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል።
የዳቦ ዋጋ ባለፈው ዓመት 5 ብር በገባበት ወቅት ብዙ ሲባል የነበረ ሲሆን በተወሰኑ ወራት ልዩነት እጥፍ በሚያስብል ደረጃ እንደጨመረ አመልክተዋል።
ሁሉም ነገር የአንድ ሰሞን የማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ይሆንና መፍትሄ ሳይሰጠው በዛው ይቀጥላል ፤ የኑሮው ጫና እጅግ እየከበደ ነው ብለዋል።
መፍትሄው ግራ የሚያጋባ ነው ያሉት አስተያየታቸውን የላኩ የቤተሰባችን አባላት ፤ የአንድ ዳቦ ዋጋ ቀስበቀስ እየጨመረ መጥቶ ወደ 10 ብር ተጠግቷል ፤ ከዚህ ቀደም ጨመረ ተብሎ ለተነሳው ሮሮ መፍትሄ ሳይሰጥ #እንድንለማመደው ተደረገ አሁንስ እንዲሁ ይቀጥላል ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ከሰሞኑን ሪፖርተር ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ከጤፍ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተው ለማደር መቸገራቸውን መገለፃቸው ይታወሳል።
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ ሰሞኑን የአንድ እንጀራ ዋጋ ቀደም ሲል ከነበረበት 17 ብር ወደ 22 እና 24 ብር ከፍ በማለቱ፣ ገዝተው ለመጠቀም መቸገራቸውን ገልጸው እንደነበር አይዘነጋም።
@tikvahethiopia