TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተን ለማደር ተቸግረናል " - ነዋሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ከጤፍ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተው ለማደር መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። ለሪፖርተር ጋዜጣ ቃላቸውን የሰጡ የከተማው ነዋሪዎች ፤ ሰሞኑን የአንድ እንጀራ ዋጋ ቀደም ሲል ከነበረበት 17 ብር ወደ 22 እና 24 ብር ከፍ በማለቱ፣ ገዝተው ለመጠቀም ተቸግረዋል፡፡ እንጀራን…
የዳቦ እና እንጀራ ዋጋ ስንት ገባ ?

በአዲስ አበባ ከተማ አካባቢዎች (የመኖሪያ መንደሮች) የአንድ ትንሹ ዳቦ ዋጋ ከወራት በፊት ከነበረበት 4 እና 5 ብር አሁን  ላይ 9 -10 ብር መድረሱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል።

የዳቦ ዋጋ ባለፈው ዓመት 5 ብር በገባበት ወቅት ብዙ ሲባል የነበረ ሲሆን በተወሰኑ ወራት ልዩነት እጥፍ በሚያስብል ደረጃ እንደጨመረ አመልክተዋል።

ሁሉም ነገር የአንድ ሰሞን የማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ይሆንና መፍትሄ ሳይሰጠው በዛው ይቀጥላል ፤ የኑሮው ጫና እጅግ እየከበደ ነው ብለዋል።

መፍትሄው ግራ የሚያጋባ ነው ያሉት አስተያየታቸውን የላኩ የቤተሰባችን አባላት ፤ የአንድ ዳቦ ዋጋ ቀስበቀስ እየጨመረ መጥቶ ወደ 10 ብር ተጠግቷል ፤ ከዚህ ቀደም ጨመረ ተብሎ ለተነሳው ሮሮ መፍትሄ ሳይሰጥ #እንድንለማመደው ተደረገ አሁንስ እንዲሁ ይቀጥላል ? ሲሉ ጠይቀዋል።

ከሰሞኑን ሪፖርተር ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ከጤፍ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተው ለማደር መቸገራቸውን መገለፃቸው ይታወሳል።

ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ ሰሞኑን የአንድ እንጀራ ዋጋ ቀደም ሲል ከነበረበት 17 ብር ወደ 22 እና 24 ብር ከፍ በማለቱ፣ ገዝተው ለመጠቀም መቸገራቸውን ገልጸው እንደነበር አይዘነጋም።

@tikvahethiopia