TIKVAH-ETHIOPIA
<unknown> – Professor_Tasew__TIKVAH
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ!
(አሐዱ ቴሌቪዥን - ኬላ ፕሮግራም)
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (AAU) መደበኛ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን በዚህ ዓመት #እንደማያስመርቅ አስታውቋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ጣሰው ወልደሃና በአሐዱ ቴሌቪዥን ከሚተላለፍ 'ኬላ' ከተሰኘ ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት ሐምሌ 4/2012 ዓ/ም በሚካሔደው የተማሪዎች ምርቃት በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የማታ የመጀመሪያ ዲግሪ ፣ የ2ኛ እና 3ኛ ድግሪ ተማሪዎች ብቻ ይካተታሉ።
በተያያዘ ዜና የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ እንዳበቃ የገጽ ለገጽ ትምህርታቸውን እንደሚቀጥሉ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር ይፋ አድርጓል።
የሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች ግን በበይነ መረብ ወይም ኦንላይን ተፈትነው ትምህርታቸውን የሚያጠናቀቁበት ሁኔታ ተቀምጧል ብሏል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
(አሐዱ ቴሌቪዥን - ኬላ ፕሮግራም)
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (AAU) መደበኛ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን በዚህ ዓመት #እንደማያስመርቅ አስታውቋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ጣሰው ወልደሃና በአሐዱ ቴሌቪዥን ከሚተላለፍ 'ኬላ' ከተሰኘ ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት ሐምሌ 4/2012 ዓ/ም በሚካሔደው የተማሪዎች ምርቃት በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የማታ የመጀመሪያ ዲግሪ ፣ የ2ኛ እና 3ኛ ድግሪ ተማሪዎች ብቻ ይካተታሉ።
በተያያዘ ዜና የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ እንዳበቃ የገጽ ለገጽ ትምህርታቸውን እንደሚቀጥሉ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር ይፋ አድርጓል።
የሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች ግን በበይነ መረብ ወይም ኦንላይን ተፈትነው ትምህርታቸውን የሚያጠናቀቁበት ሁኔታ ተቀምጧል ብሏል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia