የጄኔራል ሰዓረ መኮንን የመጨረሻ ሰዓታት
-----------------------------------------------------
(በእንግሊዝኛ የካፒታል ጋዜጣ እንደተፃፈዉ)
-------------------------------------------------------
ከአንድ የጄኔራሉ ቤተሰብ እንደተገኘዉ መረጃ የዚያች ቀን የሆነዉ ይህ ነበር፦
ሰኔ 15 በዕለተ ቅዳሜ ከምሽቱ 1 ሰዓት አካባቢ ላይ የመከላከያ ሃይል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ቦሌ ደሳለኝ ሆቴል ጀርባ በሚገኝ ቤታቸዉ እየጠበቃቸዉ የነበረዉን ጓደኛቸዉን ለማግኘት እየተቻኮሉ ከቢሯቸዉ ወጥተዉ ወደ ቤታቸዉ አቀኑ፡፡ ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ቤታቸዉ እንደደረሱ ከሳምንት በፊት የተካሄደዉን የልጃቸዉን የመዓሾ ሰዓረን ከዩኒቨርስቲ መመረቅን በማስመልከት እንኳን ደስ ያለህ ለማለት ሲጠብቃቸዉ የነበረዉን ጓደኛቸዉን ቤት ሲያገኙት አቀፉት፤ ቀጥሎም ወደ ቤታቸዉ በረንዳ በማምራት በረንዳዉ ላይ በነበሩት ሁለት ትናንሽ መቀመጫዎች ላይ ተቀመጡ፡፡
አብዛኛዉን ጊዜ ጄነራል ሰዓረ መኮንን እና ብርጋዴር ጌጀነራል ገዛኢ አበራ ሲገናኙ ሁለቱም በጋራ ተሳትፈዉባቸዉ የነበሩትን ጦርነቶች በማነሳሳት አስቂኝ ትዉስታዎቻቸዉን በማዉሳት በመሳሳቅ ያሳልፉ ነበር፡፡
ገዛኢ “ስራ በጣም ስለበዛብኝ ነዉ በልጅህ ምርቃት ላይ ያልተገኘሁት በጣም ይቅርታ ጓደኛዬ” ሲለዉ ጄነራል ሰዓረም በምላሹ ፈገግ እያለ “ችግር የለዉም” አለዉ፡፡
ከዚያም የጄኔራል ሰዓረ-ባለቤት የሆኑት ኮለኔል ጥጌ ወይን መጠጥ ካመጣችላቸዉ በኋላ ምግብ ለማምጣት ወደ ኩሺና በምትመለስበት ወቅት የሁለቱ ጄኔራሎች ህይወት በድንገት ጠፋ፡፡ መስፍን ጥጋቡ የሚባል እድሜዉ ከ25-27 የሚገመተዉ ወጣቱ የጄኔራል ሰዓረ ጠባቂ ብቻዉን ወደ መኖርያ ቤቱ በረንዳ በመምጣት መሳርያዉን ደቅኖ ጥይት አዘነበባቸዉ፡፡ ከዚያም ከፍተኛ ጩሀት አካባቢዉን አደበላለቀዉ፡፡ ኮለኔል ፅጌ ከልጃቸዉ ጋር በመሆን ከተደበቁበት ክፍል ሳይወጡ ማልቀስና መጮህ ጀመሩ፡፡ የተኩስ እሩምታ በብዛት ቢሰማም አንድም ሰዉ ዝር አላለም፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ከቤቱ ዉጪ የነበሩ ሌሎች ጠባቂዎች ሲመጡ ጄነራሎቹ መሬት ላይ ተዘርግተዉና ከፍተኛ ደም እየፈሰሳቸዉ አገኟቸዉ፡፡ በጄኔራሎቹ መሃከል ጠባቂዉ መሳፍንትም ተዘርግቶ ነበር፡፡ ቤተሰቦቹ ሁለቱንም ጄኔራሎች ይዘዉ ከምሽቱ 2፡30 አካባቢ ወደ ዋሺንግተን ሜዲካል ማዕከል ቢያቀኑም ሆስፒታሉ ሳይደርሱ ሁለቱ ጄኔራሎች አረፉ፡፡
አንድ የቤተሰቡ የቅርብ ሰዉም እንዲህ አለ “ጄኔራሎቹ ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ ከጄኔራሎቹ መካከል ተዘርግቶ የነበረዉ ጠባቂ ሁሉም ሰዉ የሞተ መስሏቸዉ ነበር ግን ሰዉዬዉ አልሞተም ነበር፡፡ የሞተ ለማስመሰል ተዘርግቶ ነበር፡፡ ነገር ግን ከዛን ተነስቶ ለመሮጥ ሞከረ፣ ሌሎቹ ጠባቂዎች ሲዩት ተኩሰዉ እግሩን መቱት፤ ከዚየም ወደ ትንሽ የጥበቃ ክፍል ሮጦ ገባ፤ ከዚያ በኋላ ሰዉዬዉ ራሱ ላይ እስኪተኩስ ድረስ ብዙ የተኩስ ልዉዉጦች ነበሩ፤ ከዚያም ጥበቃዎቹ ጎትተዉ አዉጥተዉት ወደ ሆስፒታል ወሰዱት”፡፡
ከዚህ ሁሉ ግድያ በፊት ጄኔራል ሰዓረን መኖርያ ቤት ለ4 ወራት ሲጠብቅ የነበረዉ ወታደር ከጄኔራሉ ቤት እንዲቀየር መዳቢዎችን (ሃላፊዎችን) ጠይቆ ነበር፡፡ ከዚያም ዉጪ የጄኔራሉ ባለቤት የሆኑት ኮለኔል ፅጌ የመሳፍንትን ሁኔታ ስላልወደዱት ባለቤታቸዉን (ጄኔራል ሰዓረ) ጠባቂዉን በሌላ ጠባቂ እንዲቀየር በተደጋጋሚ ቢጠይቁም ጄነራሉ ሃሳባቸዉንና ጭቅጨቃቸዉን ባለመስማት ጠባቂያቸዉን በማመን ቀጠሉ ይላል ለካፒታል ጋዜጣ የተሰጠዉ ምላሽ፡፡
Via #ኤግል_ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
-----------------------------------------------------
(በእንግሊዝኛ የካፒታል ጋዜጣ እንደተፃፈዉ)
-------------------------------------------------------
ከአንድ የጄኔራሉ ቤተሰብ እንደተገኘዉ መረጃ የዚያች ቀን የሆነዉ ይህ ነበር፦
ሰኔ 15 በዕለተ ቅዳሜ ከምሽቱ 1 ሰዓት አካባቢ ላይ የመከላከያ ሃይል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ቦሌ ደሳለኝ ሆቴል ጀርባ በሚገኝ ቤታቸዉ እየጠበቃቸዉ የነበረዉን ጓደኛቸዉን ለማግኘት እየተቻኮሉ ከቢሯቸዉ ወጥተዉ ወደ ቤታቸዉ አቀኑ፡፡ ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ቤታቸዉ እንደደረሱ ከሳምንት በፊት የተካሄደዉን የልጃቸዉን የመዓሾ ሰዓረን ከዩኒቨርስቲ መመረቅን በማስመልከት እንኳን ደስ ያለህ ለማለት ሲጠብቃቸዉ የነበረዉን ጓደኛቸዉን ቤት ሲያገኙት አቀፉት፤ ቀጥሎም ወደ ቤታቸዉ በረንዳ በማምራት በረንዳዉ ላይ በነበሩት ሁለት ትናንሽ መቀመጫዎች ላይ ተቀመጡ፡፡
አብዛኛዉን ጊዜ ጄነራል ሰዓረ መኮንን እና ብርጋዴር ጌጀነራል ገዛኢ አበራ ሲገናኙ ሁለቱም በጋራ ተሳትፈዉባቸዉ የነበሩትን ጦርነቶች በማነሳሳት አስቂኝ ትዉስታዎቻቸዉን በማዉሳት በመሳሳቅ ያሳልፉ ነበር፡፡
ገዛኢ “ስራ በጣም ስለበዛብኝ ነዉ በልጅህ ምርቃት ላይ ያልተገኘሁት በጣም ይቅርታ ጓደኛዬ” ሲለዉ ጄነራል ሰዓረም በምላሹ ፈገግ እያለ “ችግር የለዉም” አለዉ፡፡
ከዚያም የጄኔራል ሰዓረ-ባለቤት የሆኑት ኮለኔል ጥጌ ወይን መጠጥ ካመጣችላቸዉ በኋላ ምግብ ለማምጣት ወደ ኩሺና በምትመለስበት ወቅት የሁለቱ ጄኔራሎች ህይወት በድንገት ጠፋ፡፡ መስፍን ጥጋቡ የሚባል እድሜዉ ከ25-27 የሚገመተዉ ወጣቱ የጄኔራል ሰዓረ ጠባቂ ብቻዉን ወደ መኖርያ ቤቱ በረንዳ በመምጣት መሳርያዉን ደቅኖ ጥይት አዘነበባቸዉ፡፡ ከዚያም ከፍተኛ ጩሀት አካባቢዉን አደበላለቀዉ፡፡ ኮለኔል ፅጌ ከልጃቸዉ ጋር በመሆን ከተደበቁበት ክፍል ሳይወጡ ማልቀስና መጮህ ጀመሩ፡፡ የተኩስ እሩምታ በብዛት ቢሰማም አንድም ሰዉ ዝር አላለም፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ከቤቱ ዉጪ የነበሩ ሌሎች ጠባቂዎች ሲመጡ ጄነራሎቹ መሬት ላይ ተዘርግተዉና ከፍተኛ ደም እየፈሰሳቸዉ አገኟቸዉ፡፡ በጄኔራሎቹ መሃከል ጠባቂዉ መሳፍንትም ተዘርግቶ ነበር፡፡ ቤተሰቦቹ ሁለቱንም ጄኔራሎች ይዘዉ ከምሽቱ 2፡30 አካባቢ ወደ ዋሺንግተን ሜዲካል ማዕከል ቢያቀኑም ሆስፒታሉ ሳይደርሱ ሁለቱ ጄኔራሎች አረፉ፡፡
አንድ የቤተሰቡ የቅርብ ሰዉም እንዲህ አለ “ጄኔራሎቹ ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ ከጄኔራሎቹ መካከል ተዘርግቶ የነበረዉ ጠባቂ ሁሉም ሰዉ የሞተ መስሏቸዉ ነበር ግን ሰዉዬዉ አልሞተም ነበር፡፡ የሞተ ለማስመሰል ተዘርግቶ ነበር፡፡ ነገር ግን ከዛን ተነስቶ ለመሮጥ ሞከረ፣ ሌሎቹ ጠባቂዎች ሲዩት ተኩሰዉ እግሩን መቱት፤ ከዚየም ወደ ትንሽ የጥበቃ ክፍል ሮጦ ገባ፤ ከዚያ በኋላ ሰዉዬዉ ራሱ ላይ እስኪተኩስ ድረስ ብዙ የተኩስ ልዉዉጦች ነበሩ፤ ከዚያም ጥበቃዎቹ ጎትተዉ አዉጥተዉት ወደ ሆስፒታል ወሰዱት”፡፡
ከዚህ ሁሉ ግድያ በፊት ጄኔራል ሰዓረን መኖርያ ቤት ለ4 ወራት ሲጠብቅ የነበረዉ ወታደር ከጄኔራሉ ቤት እንዲቀየር መዳቢዎችን (ሃላፊዎችን) ጠይቆ ነበር፡፡ ከዚያም ዉጪ የጄኔራሉ ባለቤት የሆኑት ኮለኔል ፅጌ የመሳፍንትን ሁኔታ ስላልወደዱት ባለቤታቸዉን (ጄኔራል ሰዓረ) ጠባቂዉን በሌላ ጠባቂ እንዲቀየር በተደጋጋሚ ቢጠይቁም ጄነራሉ ሃሳባቸዉንና ጭቅጨቃቸዉን ባለመስማት ጠባቂያቸዉን በማመን ቀጠሉ ይላል ለካፒታል ጋዜጣ የተሰጠዉ ምላሽ፡፡
Via #ኤግል_ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia