ትግራይ🕊አማራ!
የትግራይ እና አማራ ክልል ክለቦች ዛሬ ባደረጉት ስብሰባ የእርስ በርስ ጨዋታዎቻቸውን በየሜዳቸው ለማድረግ ተስማምተዋል።
ዛሬ በጁፒተር ሆቴል ለሚድያዎች ዝግ በነበረው ስብሰባ የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር መኒስትር #ሒሩት_ካሳው (ዶ/ር)፣ የስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ርስቱ ይርዳው፣ የሁለቱ ክልሎች ክለብ ተወካዮች፣ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አመራሮች እና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ #ኢሳይያስ_ጂራ በመሩት ስብሰባ ሁለቱም ወገኖች የእርስ በእርስ ጨዋታዎቻቸውን በየሜዳቸው ለማድረግ ከስምምነት መድረሳቸውን ለማወቅ ተችሏል።
በዚህም መሠረት ባለፉት አምስት ሳምንታት ሊደረጉ የነበሩና ወደ ሌላ ጊዜ ተሸጋግረው የነበሩት የባህር ዳር ከተማ እና ስሑል ሽረ፣ የፋሲል ከነማ እና መቐለ 70 እንደርታ እንዲሁም የመቐለ 70 እንደርታ እና ባህር ዳር ከተማዎች በባለሜዳዎቹ ከተማ እንዲካሄድ ተስማምተዋል።
በሀገሪቱ በቅርብ ጊዜያት የተከሰተውን ፖለቲካዊ ሁኔታ ተከትሎ በሁለቱ ክልሎች ክለቦች መካከል ከኅዳር 9 ቀን 2010 ወዲህ በየሜዳቸው የእርስ በርስ ጨዋታ ተከናውኖ አያውቅም።
ምንጭ፦ ሶከር ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የትግራይ እና አማራ ክልል ክለቦች ዛሬ ባደረጉት ስብሰባ የእርስ በርስ ጨዋታዎቻቸውን በየሜዳቸው ለማድረግ ተስማምተዋል።
ዛሬ በጁፒተር ሆቴል ለሚድያዎች ዝግ በነበረው ስብሰባ የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር መኒስትር #ሒሩት_ካሳው (ዶ/ር)፣ የስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ርስቱ ይርዳው፣ የሁለቱ ክልሎች ክለብ ተወካዮች፣ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አመራሮች እና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ #ኢሳይያስ_ጂራ በመሩት ስብሰባ ሁለቱም ወገኖች የእርስ በእርስ ጨዋታዎቻቸውን በየሜዳቸው ለማድረግ ከስምምነት መድረሳቸውን ለማወቅ ተችሏል።
በዚህም መሠረት ባለፉት አምስት ሳምንታት ሊደረጉ የነበሩና ወደ ሌላ ጊዜ ተሸጋግረው የነበሩት የባህር ዳር ከተማ እና ስሑል ሽረ፣ የፋሲል ከነማ እና መቐለ 70 እንደርታ እንዲሁም የመቐለ 70 እንደርታ እና ባህር ዳር ከተማዎች በባለሜዳዎቹ ከተማ እንዲካሄድ ተስማምተዋል።
በሀገሪቱ በቅርብ ጊዜያት የተከሰተውን ፖለቲካዊ ሁኔታ ተከትሎ በሁለቱ ክልሎች ክለቦች መካከል ከኅዳር 9 ቀን 2010 ወዲህ በየሜዳቸው የእርስ በርስ ጨዋታ ተከናውኖ አያውቅም።
ምንጭ፦ ሶከር ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia