TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update የቀድሞውን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ምክትል እና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀኔራል አቶ #ያሬድ_ዘሪሁንን አስመልጠዋል በሚል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ። ዛሬ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ የወንጀል ችሎት አቶ ያሬድን አስመልጠዋል የተባሉት የነብስ አባቱ አባ ሃይለማርያም ሃይለሚካኤል እና ሾፌራቸው አሸናፊ ታደለ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪውን ለመያዝ በሚል ችሎቱን የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል። ችሎቱም መርማሪ ፖሊስ ያቀረበው ሃሳብ ተቀባይነት የለውም በሚል ፖሊስ በ10 ቀን ውስጥ #አጣርቶ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia