የ3 ዓመት ህፃን ልጅ #አግቶ ቤተሰቦቹ 500 ሺህ ብር እንዲያመጡ ሲጠይቅ የነበረው አጋች በቁጥጥር ስር ዋለ።
በአማራ ክልል፤ ማዕከላዊ ጎንደር ዞን የቆላድባ ከተማ ነዋሪ የሆነው አቶ ደጀን አረጋ የ3 ዓመት ልጅ ህፃን አማኑኤል ወንድማገኝን ከደብረ ማርቆስ ከተማ 06 ቀበሌ በማገት ወደ ጠገዴ ወረዳ እርጎየ ቀበሌ ጫካ ውስጥ ይዞ ይገባል።
ህፃኑን በጫካው ውስጥ ለ7 ቀን ያክል ይዞ ቤተሰቦቹን 500 ሺህ ብር እንዲከፍሉ ሲጠይቅ ከቆየ በኃላ ፖሊስ ባደረገው ኦፕሬሽን ህፃኑን ከአጓቾች እጅ ማስለቀቅ ችሏል።
ፖሊስ ህፃኑ ታግቶ የነበረበትን ጫካ በመክበብ እና የተኩስ ልውውጥ በማድረግ ለጊዜው ዋናው አጋች ቢያመልጥም የጉዳዩ ተባባሪ እንደሆነ የተነገረው ጣማለው አስፋ የተባለ ግለሰብ ህፃኑን እንደያዘ በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል።
ዋናው አጋች አቶ ደጀን አረጋን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው እንቅስቃሴም ግለሰቡን ሰኔ 14 በቁጥጥር ማዋል ተችሏል።
የሶሮቃ ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት ታግቶ የነበረውን ህፃን ለቤተሰቡ ካስረከበ በኃላ የማህበረሰቡ እሴትና ባህል መገለጫ ያልሆነ አፀያፊ ተግባር በዋና ተዋናይነት ፈፅሟል በሚል የተጠረጠረውን ደጀን አረጋን በቁጥጥር ስር ለማዋል የተባባሪ አጋች ጣማለው አስፋ ቤተሰቦች ጉዳዩን በዋናነት እንዲከታተሉና ጥቆማ እንዲሰጡ ማድረጉን ገልጿል።
ሌሎች ልዩ ልዩ ዘዴዎችንም በመጠቀም ባደረገው ክትትል ሰኔ 14/2015 ዓ.ም ከአካባቢው ሚሊሻና ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ጠገዴ ወረዳ እርጎየ ቀበሌ ልዩ ስሙ " እምባ ጓዳድ " ከተባለ ቦታ ደጀን አረጋን በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል።
የሶሮቃ ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤትም ጉዳዩን እያጣራ መሆኑን ያሳወቀ ሲሆን ተጠርጣሪውን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል ሲባል የአካባቢው ማህበረሰብና መላው የፀጥታ መዋቅር ላደረገው ትበብር ምስጋና አቅርቧል።
በዚህና መሰል የወንጀል ተግባራት ላይ በሚሰማሩ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ በቀጣይም በተጠናከረ መንገድ ርብርብ እንደሚደረግ አሳውቋል።
መረጃው የጠገዴ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ነው።
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል፤ ማዕከላዊ ጎንደር ዞን የቆላድባ ከተማ ነዋሪ የሆነው አቶ ደጀን አረጋ የ3 ዓመት ልጅ ህፃን አማኑኤል ወንድማገኝን ከደብረ ማርቆስ ከተማ 06 ቀበሌ በማገት ወደ ጠገዴ ወረዳ እርጎየ ቀበሌ ጫካ ውስጥ ይዞ ይገባል።
ህፃኑን በጫካው ውስጥ ለ7 ቀን ያክል ይዞ ቤተሰቦቹን 500 ሺህ ብር እንዲከፍሉ ሲጠይቅ ከቆየ በኃላ ፖሊስ ባደረገው ኦፕሬሽን ህፃኑን ከአጓቾች እጅ ማስለቀቅ ችሏል።
ፖሊስ ህፃኑ ታግቶ የነበረበትን ጫካ በመክበብ እና የተኩስ ልውውጥ በማድረግ ለጊዜው ዋናው አጋች ቢያመልጥም የጉዳዩ ተባባሪ እንደሆነ የተነገረው ጣማለው አስፋ የተባለ ግለሰብ ህፃኑን እንደያዘ በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል።
ዋናው አጋች አቶ ደጀን አረጋን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው እንቅስቃሴም ግለሰቡን ሰኔ 14 በቁጥጥር ማዋል ተችሏል።
የሶሮቃ ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት ታግቶ የነበረውን ህፃን ለቤተሰቡ ካስረከበ በኃላ የማህበረሰቡ እሴትና ባህል መገለጫ ያልሆነ አፀያፊ ተግባር በዋና ተዋናይነት ፈፅሟል በሚል የተጠረጠረውን ደጀን አረጋን በቁጥጥር ስር ለማዋል የተባባሪ አጋች ጣማለው አስፋ ቤተሰቦች ጉዳዩን በዋናነት እንዲከታተሉና ጥቆማ እንዲሰጡ ማድረጉን ገልጿል።
ሌሎች ልዩ ልዩ ዘዴዎችንም በመጠቀም ባደረገው ክትትል ሰኔ 14/2015 ዓ.ም ከአካባቢው ሚሊሻና ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ጠገዴ ወረዳ እርጎየ ቀበሌ ልዩ ስሙ " እምባ ጓዳድ " ከተባለ ቦታ ደጀን አረጋን በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል።
የሶሮቃ ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤትም ጉዳዩን እያጣራ መሆኑን ያሳወቀ ሲሆን ተጠርጣሪውን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል ሲባል የአካባቢው ማህበረሰብና መላው የፀጥታ መዋቅር ላደረገው ትበብር ምስጋና አቅርቧል።
በዚህና መሰል የወንጀል ተግባራት ላይ በሚሰማሩ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ በቀጣይም በተጠናከረ መንገድ ርብርብ እንደሚደረግ አሳውቋል።
መረጃው የጠገዴ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ነው።
@tikvahethiopia
👍1.83K❤192😢140👎62🕊29🙏28😱27🥰10