TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አሽከርካሪዎች_ጥንቃቄ_እያደረጋችሁ

በዛሬዉ ዕለት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሰዎች ህይወት አለፈ።

አደጋዉ የደረሰዉ በምስራቅ ጎጃም ዞን እናርጅ እናዉጋ ወረዳ ደያጠባ ቀበሌ ነው።

ከረፋዱ 5:00 ሰዓት ላይ ከሞጣ ወደ ብቸና ከተማ በመጓዝ ላይ የነበረ ኮድ (3) 78101አአ ሃይሉክስ እና ከደብረወርቅ ወደ ፈለገ ብርሃን ከተማ በመጓዝ ላይ የነበረ ኮድ (3) 16049 አማ የሆነ ዶልፊን የህዝብ ማመላለሻ መኪና እናርጅ እናዉጋ ወረዳ ደያጠባ ቀበሌ በመጋጨታቸው የሀይሉክሱን ሾፌር ጨምሮ የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ዋና ክፍል ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ልጅአዱኛ ሙሉጌታ እንደገለጽት ሌሎች አደጋ የደረሰባቸዉ 3 ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፤ ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎችም በደብረወርቅ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እየተረዱ መሆኑን ገልፀዋል።

የአደጋዉ መንስኤ እየተጣራ መሆኑ ተገልጿል።

በተለይ በዓላት በሚቃረቡበት ግዜ እና የበዓል ዕለት አሽከርካሪዎች ፍጥነታቸውን በመቀነስ እና አደጋን ተከላክሎ የማሽከርከር ብቃትን በማሳደግ በአጠቃላይ ለአደጋ በማይዳርግ ሁኔታ በማሽከርከር የራስ ህይወት እና የዜጎችን ህይወት ከሞት መታደግ ይገባል በማለት አሳስበዋል።

መረጃው የደረሰን ከምሥራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ ነው።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
👍1