TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኦነግ⬇️

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ #ዳውድ_ኢብሳ ድርጅታቸው #ትጥቁን ለመፍትት ከመንግስት ጋር አለመስማማቱን ተናገሩ። አቶ ዳውድ ከዋልታ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ"ኦነግ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው ትጥቅ ፈተኖ ነው የሚለውን መረጃ አስተባብለዋል።

አቶ ዳውድ ለዋልታ ሲናገሩ "እኛ ትጥቅ እንድንፈታ የተስማማንበት ስምምነት የለም። #የታጠቀው አካል ትጥቅ #ይዞ እያለ እኛ ትጥቅ #የምንፈታበት ምክንያት የለም።" ብለዋል። አክለውም "ትጥቅ መፍታት የሚባል sensitivity ጥያቄ ነው። ትጥቅ ፈቱ መባልም አንፈልግም። ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚመጣው አንዱ ትጥቅ የሚፈታ አንዱ ትጥቅ የሚያስፈታ ይመስላል። የሀገሪቱ ሰላም እንዲጠበቅ ኦነግ ያለው ሚና ምን እንደሚሆን ነው የተስማማነው።" ሲሉ ለዋልታ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አቶ ዳውድ ሰኔ 16 በጠቅላ ሚንስትሩ ላይ በተደረገው #የግድያ ሙከራ ድርጅታቸው እንዳልተሳተፈ ገልፀዋል። በቡራዩና በአዲስ አበባ በተፈጠሩ ግጭቶችም ኦነግ አለመሳተፉን ሊቀመንበሩ ገልፀዋል።

አቶ ዳውድ በበደኖና በአርባ ጉጉ በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰው ጭፍጨፋ #በገለልተኛ አካል #እንዲጣራ የኦነግ ፍላጎት መሆኑን አንስተዋል።

#TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia