TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኢቦላ‼️

በዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፖብሊክ ኢቦላን ለመላከል እየተከናወነ ያለውን ስራ ለጋሾች እንዲደገፉ የአለም ጤና ድርጅት ጠየቀ፡፡

የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር #ቴድሮስ_አድሀኖም የገንዘብ እጥረት ቁልፍ ውጤቶችን እንዳይሸረሸራቸው ስጋት መኖሩን ተናግረዋል፡፡

ከስፍራ ወደ ስፍራ የሚንቀሳቀስ ማህበረሰብ ባለበት አካባቢ ያለው የጤና ስርአት ክፍተት እና የፀጥታ ሁኔታ ሌሎች ፈተናዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

በሀገሪቱ በኢቦላ የተጠቁትን ቡቴምቦና እና ካትዋን ለመመልከት እንዲሁም ከአዲሱ ኘሬዚዳንት ፊሊክስ ተሲኬዳ ጋር ለመነጋገር ቀጠሮ መያዛቸውን ዶክተር ቴድሮስ አስታውቀዋል፡፡

በሀገሪቱ የሚከናወነውን የመከላከል ስራ ለማጠናከር የሚያግዝ የግብአት ድጋፍ መላኩንም አስታውቀዋል፡፡

በኮንጎ የተከሰተውን ኢቦላን ለመከላከል የአለም ጤና ድርጅት ከጠየቀው የ1መቶ 48 ሚሊዮን ዶላር አለም አቀፍ ድጋፍ እስካሁን ያገኘው ከ1ዐ ሚሊዮን ዶላር የዘለለ አይደለም፡፡

በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ የደረሰውን ትግል ውጤታማ ለማድረግ የለጋሾች ድጋፍ ለአለም ጤናማነት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩበት እንደሆነ ዶክተር ቴድሮስ አስገንዝበዋል፡፡

ምንጭ፡- ሲጂቲኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia