TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ከቡራዩ ከተፈናቀሉ ዜጎች በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ #ተፈናቃይ ዜጎች ቁጥር 1 ሺህ 514 ብቻ ናቸው፡፡ በቡራዩ በአሁኑ ወቅት በተፈጠረው #መረጋጋት በአዲስ አበባ ጊዜያዊ የመጠለያ ጣቢያዎች ተጠልለው ከነበሩ 11 ሺህ 902 ያህሉ ወደመጡበት የመኖሪያ ቀያቸው በአዲስ አበባ አስተዳደር አማካይነት ተመልሰዋል፡፡

©የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ICRC #Tigray የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በተለያዩ ክልሎች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ማድረጉን ቀጥሏል። ኮሚቴው #በትግራይ_ክልል በግጭት የተጎዱ አርሶ አደሮችን ምርታማነት ለማሳደግ ፦ 👉 በማዕከላዊ፣ 👉 በምስራቅ ፣ 👉 በደቡብ ምስራቅ እና በደቡብ ዞኖች ለሚገኙ ለ20,000 አባውራዎች (120,000 ግለሰቦች) የአፈር ማዳበሪያ በማከፋፈል ላይ እንደሚገኝ ዛሬ አሳውቋል።…
#ICRC

ICRC ለተፈናቃይ አባወራዎች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በግጭት የተፈናቀሉ አብዛኛዎቹ ሰዎች በሕይወት ለመቆየት በሰብአዊ እርዳታ ላይ ጥገኛ መሆናቸውን አመልክቷል።

በመጠለያ ካምፖች ውስጥ ያሉ ተፈናቃይ ሰዎች ደግሞ ምንም አይነት አስተማማኝ የኢኮኖሚ ምንጭ የላቸውም ሲል ገልጿል።

በዚህም ምክንያት በአማራ ክልል ፦ ሰሜን ወሎ ዞን፣ ሃብሩ ወረዳ፣ ጃራ የተፈናቃዮች መጠለያ ካምፕ ለሚገኙ 3,674 #ተፈናቃይ_አባወራዎች (22,044 ግለሰቦች) መሰረታዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት የሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
👍24916👏12😢5🥰3🙏3