TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ደብዛው የጠፋው ጋዜጠኛ⬇️

የቱርክ ፕሬዚዳንት #ጣይብ_ኤርዶሃንና የሳዑዲው ንጉስ #ሳልማን_ቢን አብዱልአዚዝ ደብዛው በጠፋው ጋዜጠኛ ጉዳይ ላይ በስልክ #ተወያዩ

ጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጊ ከሁለት ሳምንት በፊት ቱርክ በሚገኘው የሳዑዲ ዓረቢያ ኮንስላ ጽህፈት ቤት ጉዳይ #ሊያስፈፅም እንደገባ ደብዛው ከጠፋ 13 ቀናት ተቆጥረዋል።

የቱርክ ፕሬዚዳንት ጣይብ ኤርዶሃንና የሳዑዲው ንጉስ ሳልማን ትናንት ሌሊት በስልክ ባደረጉት ውይይት የጋዜጠኛው መጥፋት ጉዳይ አጀንዳቸው ነበር ተብሏል።

ኤርዶሃን በጀማል ካሾጊ ጉዳይ ላይ ጥምር ቡድን ተቋቁሞ ምርመራ እንዲካሄድ በአፅንኦት መናገራቸው ተሰምቷል።

ካሾጊ በሳዑዲ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በነበረበት ወቅት 10 ሳዑዲዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት በሁለት አውሮፕላኖች ወደ ኢስታንቡል በማምራት ጽህፈት ቤቱን በተመሳሳይ ቀን መጎብኘታቸውን የቱርክ ፖሊስ መረጃዎች ያሳያሉ።

የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ አምደኛ የሆነው የሳዑዲ ዜግነት ያለው ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ የት እንደገባ አለመታወቁን ተከትሎ ቱርክ፣ አሜሪካ እና ብሪታኒያ ከሳዑዲ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ቱርክ ጋዜጠኛው #መገደሉን የሚያሳዩ መረጃዎችን አግኝቻለሁ እያለች ነው።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዳሉት ጋዜጠኛው በቆንስላ ጽህፈት ቤቱ ውስጥ መገደሉ ከተረጋገጠ ሳዑዲ ከባድ #ቅጣት ይጠብቃታል ብለዋል።

ይህን ተከትሎም ሳዑዲ በሰጠችው ምላሽ ማንኛውም ሀገር በጀማል ካሾጊ ጉዳይ ሀሰተኛ ውንጀላ የሚያቀርብ፣ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የሚያስብ ሀገር ካለ የአፀፋ ምላሽ እንደምትወስድ አስጠንቅቃለች።

ምንጭ፦ አናዶሉና ሮይተርስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
1