የኢትዮ ቴሌኮም እና ገቢዎች ሚኒስቴር ስምምነት !
ኢትዮ ቴሌኮም እና በገቢዎች ሚኒስቴር መካከል #የግብር_ክፍያዎችን በቴሌብር ለመሰብሰብ የሚያስችል ስምምነት ዛሬ አድርገዋል።
ስምምነቱ የሚኒስቴር መ/ቤቱ ደንበኞች የተለያዩ የግብር ክፍያዎችን በቴሌብር የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ተጠቅመው #በየትኛውም_ጊዜ እና #ቦታ ሆነው ያለምንም ውጣውረድ በኦንላይን አገልግሎት እንዲፈጽሙ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡
አጭር መረጃ ስለ ስምምነቱ፦
- በዋናነት ለገቢዎች ሚኒስቴር የገቢ ግብርንና የግል ሠራተኞች የጡረታ መዋጮ፣ የፌደራል ታክስ ክፍያዎችን በወቅቱ ለመሰብሰብ ያግዛል።
- የቴሌብር ተጠቃሚዎች ከግል ወይም ከድርጅት የቴሌብር አካውንታቸው በቴሌብር የሞባይል መተግበሪያ/ በአጭር ቁጥር *127# በመጠቀም የግብር ክፍያቸውን ባሉበት ቦታ ሆነው በቀላሉ ለመክፈል ያስችላቸዋል።
- በቴሌብር ግብይት የሚፈጽሙ ነጋዴዎች ከሚፈጽሟቸው ግብይቶች ከሰበስቡት ገንዘብ ላይ ለግብር ክፍያ በቀጥታ መክፈል ይችላሉ።
- በገቢዎች ሚኒስቴር ሰርቨር ላይ መረጃን ወቅታዊ በማድረግ በመዘግየት ምክንያት በግብር ከፋዩ ላይ የሚደርሰውን ቅጣት ለማስቀረት እና ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል።
- አገልግሎቱን ለማግኘት የሚኒስቴር መ/ቤቱ ደንበኞች ወደ www.mor.gov.et. በመግባት እና የኤሌክትሮኒክ ታክስ አገልግሎት የሚለውን በመመምረጥ፣ አስፈላጊውን ሂደት ሲጨርሱ ከገቢዎች ሚኒስቴር የሚሰጣቸውን የሰነድ ቁጥር በመጠቀም በቀላሉ ክፍያቸውን በቴሌብር አፕሊኬሽን መፈጸም ይችላሉ።
- በአጭር ቁጥር *127# በመጠቀም የግብር ክፍያ የሚለውን በመምረጥ ክፍያ መፈፀም ይቻላል።
- ደንበኞች የክፍያ ደረሰኝ ወዲያውኑ በኢ-ሜል አድራሻቸው ማግኘት ይቻሉ።
Credit : አዲስ ማለዳ
Photo Credit : የገቢዎች ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
ኢትዮ ቴሌኮም እና በገቢዎች ሚኒስቴር መካከል #የግብር_ክፍያዎችን በቴሌብር ለመሰብሰብ የሚያስችል ስምምነት ዛሬ አድርገዋል።
ስምምነቱ የሚኒስቴር መ/ቤቱ ደንበኞች የተለያዩ የግብር ክፍያዎችን በቴሌብር የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ተጠቅመው #በየትኛውም_ጊዜ እና #ቦታ ሆነው ያለምንም ውጣውረድ በኦንላይን አገልግሎት እንዲፈጽሙ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡
አጭር መረጃ ስለ ስምምነቱ፦
- በዋናነት ለገቢዎች ሚኒስቴር የገቢ ግብርንና የግል ሠራተኞች የጡረታ መዋጮ፣ የፌደራል ታክስ ክፍያዎችን በወቅቱ ለመሰብሰብ ያግዛል።
- የቴሌብር ተጠቃሚዎች ከግል ወይም ከድርጅት የቴሌብር አካውንታቸው በቴሌብር የሞባይል መተግበሪያ/ በአጭር ቁጥር *127# በመጠቀም የግብር ክፍያቸውን ባሉበት ቦታ ሆነው በቀላሉ ለመክፈል ያስችላቸዋል።
- በቴሌብር ግብይት የሚፈጽሙ ነጋዴዎች ከሚፈጽሟቸው ግብይቶች ከሰበስቡት ገንዘብ ላይ ለግብር ክፍያ በቀጥታ መክፈል ይችላሉ።
- በገቢዎች ሚኒስቴር ሰርቨር ላይ መረጃን ወቅታዊ በማድረግ በመዘግየት ምክንያት በግብር ከፋዩ ላይ የሚደርሰውን ቅጣት ለማስቀረት እና ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል።
- አገልግሎቱን ለማግኘት የሚኒስቴር መ/ቤቱ ደንበኞች ወደ www.mor.gov.et. በመግባት እና የኤሌክትሮኒክ ታክስ አገልግሎት የሚለውን በመመምረጥ፣ አስፈላጊውን ሂደት ሲጨርሱ ከገቢዎች ሚኒስቴር የሚሰጣቸውን የሰነድ ቁጥር በመጠቀም በቀላሉ ክፍያቸውን በቴሌብር አፕሊኬሽን መፈጸም ይችላሉ።
- በአጭር ቁጥር *127# በመጠቀም የግብር ክፍያ የሚለውን በመምረጥ ክፍያ መፈፀም ይቻላል።
- ደንበኞች የክፍያ ደረሰኝ ወዲያውኑ በኢ-ሜል አድራሻቸው ማግኘት ይቻሉ።
Credit : አዲስ ማለዳ
Photo Credit : የገቢዎች ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
👍798👎100❤31😱23🕊16🙏13😢12🥰9🤔8