#ብሄራዊ_ቤተ_መንግስት
የ2011 በጀት ዓመት የታማኝ የግብር ከፋዮች የሽልማትና የእውቅና መድረክ በብሄራዊ ቤተ-መንግስት ተካሂዷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ፣ የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ፕሮግራሙን ታድመዋል።
“ሀገረን መውደድ በተግባር ነው” በሚል መሪ ቃል ነው መርሃ ግበሩ የተካሄደው። ወ/ሮ አዳነች በመክፈቻ ንግግራቸው በ2011 በጀት ዓመት 198.2 ቢሊዮን ብር የግብር ገቢ መሰብሰቡን ገልፀዋል።
በበጀት ዓመቱ በተለያዩ አካባቢዎች በቁጥጥር ስር ከዋሉ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችም 1.6 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡንም ተናግረዋል። በመጨረሻም በበጀት ዓመቱ በታማኝ ግብር ከፋይነት ለተመረጡ 163 ተቋማት በዕለቱ የክብር እንግዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አማካይነት እውቅናና ሽልማት ተበርክቷል።
Via #etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የ2011 በጀት ዓመት የታማኝ የግብር ከፋዮች የሽልማትና የእውቅና መድረክ በብሄራዊ ቤተ-መንግስት ተካሂዷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ፣ የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ፕሮግራሙን ታድመዋል።
“ሀገረን መውደድ በተግባር ነው” በሚል መሪ ቃል ነው መርሃ ግበሩ የተካሄደው። ወ/ሮ አዳነች በመክፈቻ ንግግራቸው በ2011 በጀት ዓመት 198.2 ቢሊዮን ብር የግብር ገቢ መሰብሰቡን ገልፀዋል።
በበጀት ዓመቱ በተለያዩ አካባቢዎች በቁጥጥር ስር ከዋሉ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችም 1.6 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡንም ተናግረዋል። በመጨረሻም በበጀት ዓመቱ በታማኝ ግብር ከፋይነት ለተመረጡ 163 ተቋማት በዕለቱ የክብር እንግዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አማካይነት እውቅናና ሽልማት ተበርክቷል።
Via #etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia