በምዕራብ ኦሮሚያ በነበረው #ሁከት ተሳትፈዋል የተባሉ የመንግስት አመራሮች እየተመረመሩ ነው!
.
.
.
በምዕራብ ኦሮሚያ ዞኖች ባለፉት ወራት በነበረው የፀጥታ ቀውስ ሀላፊነታቸውን አልተወጡም ተሳትፎም አድርገዋል ተብለው የተጠረጠሩ አንድ መቶ ያህል የክልሉ አመራሮችና የፀጥታ አካላት ላይ ምርመራ እየተካሄደ ሲሆን ስምንት መቶ የሚጠጉ ፖሊሶችም ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ ነው።
ባለፉት ወራት የምዕራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋ ፤ ሆሮ ጉዱሩ እና ቄለም አካባቢዎች በኦሮሞ ነፃነት ግንባር ታጣቂዎችና በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች መካከል ከፍተኛ ግጭት እንደነበረ ይታወሳል። በዚህ ግጭት ደግሞ የዞኑ አመራሮችን ከመግደል እስከ ባንኮች ዘረፋ የሚደርስ ሰፊ ወንጀል መፈጸሙ በክልሉ መንግስት መግለጫ የተሰጠበት እንደነበርም አይዘነጋም፡፡በተለይ አባቶርቤ ተብሎ የሚጠረ ህቡዕ ቡድን የተለያዩ ግለሰቦችን በመግደል ድርጊት ተሰማርቶ እንደነበርም መንግስት ራሱ ይፋ አድርጓል።
አሁን አካባቢው ላይ በኦሮሞ ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) እና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) መካከል የተፈጸመውን እርቅ ተከትሎ አንጻራዊ ሰላም የወረደ መስሏል፡፡ ሁለቱን ወገኖች በማሸማገል ስራ ላይ የነበሩት አባ ገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎችም( እናቶች) ውጥረት እና ግጭት ሲንጣቸው በነበሩ ዞኖች ተንቀሳቅሰው ባሳለፍነው ሳምንት ሁኔታውን መቃኘታቸው ይታወቃል፡፡ ታጥቀው የነበሩ የኦነግ አባላትንም ትጥቅ በማስፈታት ወደተዘጋጀላቸው ካምፕ እንዲገቡ እየተደረገ ነው። ከሁሉም በላይ ግን የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ እና የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ #ለማ_መገርሳ አካባቢው ድረስ በመጓዝ ያደረጉት ጉብኝት እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር የነበራቸው ውይይት ይበልጥ በስፍራው የሰላም አየር መንፈስ መጀመሩን ለማመላከት የታሰበ ይመስላል፡፡
አሁን ይህ ውጤት ይገኝ እንጂ ለወራት የተስተዋለውን ግጭት ያባባሰው እና ለቁጥጥር አዳጋች ያደረገው ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ የክልሉ የጸጥታ አካላት #በሁከቱ መሳተፋቸው መሆኑን ዋዜማ ሬድዮ መረጃ አግኝቻለሁ ብሏል፡፡ በተለይ አባቶርቤ ተብሎ ሲንቀሳቀስ በነበረው የህቡዕ ቡድን ውስጥም ሆነ አከባቢው ላይ በነበረው ሁከት የቀጥታ ተሳትፎ ነበራቸው ተብለው የተጠረጠሩ ከ800 በላይ የኦሮሚያ ክልል የፖሊስ አባላት በአሁኑ ወቅት አምቦ በሚገኘው ሰንቀሌ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የተሃድሶ ስልጠና እየተሰጣቸው እንደሚገኝም ጭምር ነው ራድዮ ጣቢያው አረጋግጫለሁ ብሎ የዘገበው፡፡
ዋዜማ ራድዮ ከምንጮቼ ሰማሁ እንዳለው ይበልጥ #ሁከቱን_በመምራት በማደራጀትና በማስተባበር #አባቶርቤ በተሰኘው ቡድን ውስጥም በቀጥታ በመሳተፍ ደግሞ በ100 ግለሰቦች ላይ ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል፡፡ ከነዚህ መካከልም #የዞን_አመራሮች እና #በፖሊስ_አመራርነት ደረጃ የሚገኙ መኖራቸው ጭምርም ታውቋል፡፡
አካባቢውን ያረጋጋሉ ተብለው ከአዲስ አበባ የተላኩት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራርም #ተጠርጥረው በምርመራ ላይ ናቸው፡፡
ምንጭ፦ ዋዜማ ራዲዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
.
በምዕራብ ኦሮሚያ ዞኖች ባለፉት ወራት በነበረው የፀጥታ ቀውስ ሀላፊነታቸውን አልተወጡም ተሳትፎም አድርገዋል ተብለው የተጠረጠሩ አንድ መቶ ያህል የክልሉ አመራሮችና የፀጥታ አካላት ላይ ምርመራ እየተካሄደ ሲሆን ስምንት መቶ የሚጠጉ ፖሊሶችም ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ ነው።
ባለፉት ወራት የምዕራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋ ፤ ሆሮ ጉዱሩ እና ቄለም አካባቢዎች በኦሮሞ ነፃነት ግንባር ታጣቂዎችና በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች መካከል ከፍተኛ ግጭት እንደነበረ ይታወሳል። በዚህ ግጭት ደግሞ የዞኑ አመራሮችን ከመግደል እስከ ባንኮች ዘረፋ የሚደርስ ሰፊ ወንጀል መፈጸሙ በክልሉ መንግስት መግለጫ የተሰጠበት እንደነበርም አይዘነጋም፡፡በተለይ አባቶርቤ ተብሎ የሚጠረ ህቡዕ ቡድን የተለያዩ ግለሰቦችን በመግደል ድርጊት ተሰማርቶ እንደነበርም መንግስት ራሱ ይፋ አድርጓል።
አሁን አካባቢው ላይ በኦሮሞ ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) እና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) መካከል የተፈጸመውን እርቅ ተከትሎ አንጻራዊ ሰላም የወረደ መስሏል፡፡ ሁለቱን ወገኖች በማሸማገል ስራ ላይ የነበሩት አባ ገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎችም( እናቶች) ውጥረት እና ግጭት ሲንጣቸው በነበሩ ዞኖች ተንቀሳቅሰው ባሳለፍነው ሳምንት ሁኔታውን መቃኘታቸው ይታወቃል፡፡ ታጥቀው የነበሩ የኦነግ አባላትንም ትጥቅ በማስፈታት ወደተዘጋጀላቸው ካምፕ እንዲገቡ እየተደረገ ነው። ከሁሉም በላይ ግን የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ እና የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ #ለማ_መገርሳ አካባቢው ድረስ በመጓዝ ያደረጉት ጉብኝት እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር የነበራቸው ውይይት ይበልጥ በስፍራው የሰላም አየር መንፈስ መጀመሩን ለማመላከት የታሰበ ይመስላል፡፡
አሁን ይህ ውጤት ይገኝ እንጂ ለወራት የተስተዋለውን ግጭት ያባባሰው እና ለቁጥጥር አዳጋች ያደረገው ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ የክልሉ የጸጥታ አካላት #በሁከቱ መሳተፋቸው መሆኑን ዋዜማ ሬድዮ መረጃ አግኝቻለሁ ብሏል፡፡ በተለይ አባቶርቤ ተብሎ ሲንቀሳቀስ በነበረው የህቡዕ ቡድን ውስጥም ሆነ አከባቢው ላይ በነበረው ሁከት የቀጥታ ተሳትፎ ነበራቸው ተብለው የተጠረጠሩ ከ800 በላይ የኦሮሚያ ክልል የፖሊስ አባላት በአሁኑ ወቅት አምቦ በሚገኘው ሰንቀሌ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የተሃድሶ ስልጠና እየተሰጣቸው እንደሚገኝም ጭምር ነው ራድዮ ጣቢያው አረጋግጫለሁ ብሎ የዘገበው፡፡
ዋዜማ ራድዮ ከምንጮቼ ሰማሁ እንዳለው ይበልጥ #ሁከቱን_በመምራት በማደራጀትና በማስተባበር #አባቶርቤ በተሰኘው ቡድን ውስጥም በቀጥታ በመሳተፍ ደግሞ በ100 ግለሰቦች ላይ ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል፡፡ ከነዚህ መካከልም #የዞን_አመራሮች እና #በፖሊስ_አመራርነት ደረጃ የሚገኙ መኖራቸው ጭምርም ታውቋል፡፡
አካባቢውን ያረጋጋሉ ተብለው ከአዲስ አበባ የተላኩት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራርም #ተጠርጥረው በምርመራ ላይ ናቸው፡፡
ምንጭ፦ ዋዜማ ራዲዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" ግድያውን የፈፀመው የፖሊስ አባል ነው " - የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን
በአዲስ አበባ ከተማ ፤ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ 8 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አባቸው አሞኜ የእለት ከእለት ተግባራቸውን በማከናወን ላይ እንዳሉ ግንቦት 4 ቀን 2015 ዓ/ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ላይ #በፖሊስ አባል መገደላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳወቀ።
ግድያውን የፈፀመው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የካሳንቺስ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት የቀጠና ኦፊሰር የሆነ አባል መሆኑን ፓሊስ ገልጿል።
እንደ ፖሊስ መረጃ ግድያውን የፈፀመው ግለሰብ ፤ የግል ጉዳዩ እንዲፈፀምለት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለወረዳ 8 አስተዳደር ጽ/ቤት ያመለክታል፡፡
ወረዳው ጉዳዩን ተመልክቶ ምላሽ እንደሚሰጠው የተገለፀለት ቢሆንም " ጥያቄዬ እንዳይፈፀም የከለከልከው አንተነህ " በሚል ምክንያት የወረዳውን ዋና ስራ አስፈፃሚ ቢሯቸው ውስጥ በስራ ላይ እንዳሉ በታጠቀው ሽጉጥ ገድሏቸዋል።
ወንጀሉን የፈፀመው የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራው እየተጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
@tikvahethiopia
" ግድያውን የፈፀመው የፖሊስ አባል ነው " - የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን
በአዲስ አበባ ከተማ ፤ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ 8 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አባቸው አሞኜ የእለት ከእለት ተግባራቸውን በማከናወን ላይ እንዳሉ ግንቦት 4 ቀን 2015 ዓ/ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ላይ #በፖሊስ አባል መገደላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳወቀ።
ግድያውን የፈፀመው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የካሳንቺስ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት የቀጠና ኦፊሰር የሆነ አባል መሆኑን ፓሊስ ገልጿል።
እንደ ፖሊስ መረጃ ግድያውን የፈፀመው ግለሰብ ፤ የግል ጉዳዩ እንዲፈፀምለት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለወረዳ 8 አስተዳደር ጽ/ቤት ያመለክታል፡፡
ወረዳው ጉዳዩን ተመልክቶ ምላሽ እንደሚሰጠው የተገለፀለት ቢሆንም " ጥያቄዬ እንዳይፈፀም የከለከልከው አንተነህ " በሚል ምክንያት የወረዳውን ዋና ስራ አስፈፃሚ ቢሯቸው ውስጥ በስራ ላይ እንዳሉ በታጠቀው ሽጉጥ ገድሏቸዋል።
ወንጀሉን የፈፀመው የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራው እየተጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
@tikvahethiopia
👍1.77K😢794❤202👎161🕊84😱74🥰37🙏19
#AddisAbaba
" ኮንስታብል ማክቤል ሮባ የተባለ የፖሊስ አባል ለስራ በታጠቀው ታጣፊ ክላሽ በተኮሰው ጥይት ነው የዶ/ር እስራኤል ጥላሁን ህይወት ያለፈው " - ፖሊስ
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን የተባለ የጤና ባለሞያ በተተኮሰበት ጥይት ተመቶ #ተገድሏል።
ግድያው የተፈፀመው #በፖሊስ_አባል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሳውቋል።
ፖሊስ ስለጉዳዩ ምን አለ ?
የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰሞኑን " ቦሌ አትላስ " አካባቢ ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን በተባለ ግለሰብ ላይ ተፈፅሟል ከተባለው የግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጿል።
ፖሊስ ምርመራ መዝገቡን ዋቢ አድርጎ እንዳስረዳው በቀን 28/3/2016 ዓ.ም ከንጋቱ 11:20 ሰአት ላይ ነው ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን ወንጀሉ የተፈጸመበት።
ወንጀሉ የተፈፀመው ወረዳ 4 ልዩ ስሙ " አዲስ ህይወት ሆስፒታል " አካባቢ ነው ብሏል።
ዶክተር እስራኤል ያሽከረክራት የነበረችው ተሽከርካሪ ኮድ 3 የሰሌዳ ቁጥር 36734 አ.አ ሲሆን፤ በወቅቱ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 የሰሌዳ ቁጥር 28177 የሆነ #ቪትስ ተሽከርካሪ የያዘ ግለሰብ የመኪና " መስታወት - ስፖኪዮ ገጭቶ አመለጠኝ " በሚል ከፍተኛ ድምጽ እያሰማ ከኋላ ይከተለው ነበር፡፡
ወደ 11፡20 አካባቢም " ፋሲካ የመኪና መሸጫ " የሚባል ቦታ ሲደርስ፤ በአካባቢው ያሉ ኑሯቸውን ጎዳና ላይ ያደረጉ ዜጎች " ያዘው ያዘው " የሚል ድምጽ በማሰማት ከፍተኛ ግርግርና ወከባ ሲፈጥሩ፤ በዚያን ሰአት #ኮንስታብል_ማክቤል_ሮባ የተባለ የፖሊስ አባል፤ ለስራ በታጠቀው ታጣፊ ክላሽ " የመኪናውን ጎማውን መትቼ ለማስቆም " በሚል በተኮሰው ጥይት የዶ/ር እስራኤል ህይወት ሊያልፍ ችሏል ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስረድቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ አንዳንድ ግዜ ወዲያውኑ መረጃ የማይሰጠው #ከምርመራ_ሂደቱ ጋር በተያያዘ የሚበላሹ ነገሮች ስለሚኖሩ ነው ያለ ሲሆን ቀጣይ የምርመራ መዝገቡ እየታየ መረጃዎችን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የትርታ ኤፍ ኤም 97.6 ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ መሆኑን ያሳውቃል።
* በጉዳዩ ላይ ከሟች ቤተሰቦች / ከቅርብ ጓደኞች መረጃ የሚገኝ ከሆነ ተከታትለን እናቀርባለን።
@tikvahethiopia
" ኮንስታብል ማክቤል ሮባ የተባለ የፖሊስ አባል ለስራ በታጠቀው ታጣፊ ክላሽ በተኮሰው ጥይት ነው የዶ/ር እስራኤል ጥላሁን ህይወት ያለፈው " - ፖሊስ
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን የተባለ የጤና ባለሞያ በተተኮሰበት ጥይት ተመቶ #ተገድሏል።
ግድያው የተፈፀመው #በፖሊስ_አባል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሳውቋል።
ፖሊስ ስለጉዳዩ ምን አለ ?
የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰሞኑን " ቦሌ አትላስ " አካባቢ ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን በተባለ ግለሰብ ላይ ተፈፅሟል ከተባለው የግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጿል።
ፖሊስ ምርመራ መዝገቡን ዋቢ አድርጎ እንዳስረዳው በቀን 28/3/2016 ዓ.ም ከንጋቱ 11:20 ሰአት ላይ ነው ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን ወንጀሉ የተፈጸመበት።
ወንጀሉ የተፈፀመው ወረዳ 4 ልዩ ስሙ " አዲስ ህይወት ሆስፒታል " አካባቢ ነው ብሏል።
ዶክተር እስራኤል ያሽከረክራት የነበረችው ተሽከርካሪ ኮድ 3 የሰሌዳ ቁጥር 36734 አ.አ ሲሆን፤ በወቅቱ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 የሰሌዳ ቁጥር 28177 የሆነ #ቪትስ ተሽከርካሪ የያዘ ግለሰብ የመኪና " መስታወት - ስፖኪዮ ገጭቶ አመለጠኝ " በሚል ከፍተኛ ድምጽ እያሰማ ከኋላ ይከተለው ነበር፡፡
ወደ 11፡20 አካባቢም " ፋሲካ የመኪና መሸጫ " የሚባል ቦታ ሲደርስ፤ በአካባቢው ያሉ ኑሯቸውን ጎዳና ላይ ያደረጉ ዜጎች " ያዘው ያዘው " የሚል ድምጽ በማሰማት ከፍተኛ ግርግርና ወከባ ሲፈጥሩ፤ በዚያን ሰአት #ኮንስታብል_ማክቤል_ሮባ የተባለ የፖሊስ አባል፤ ለስራ በታጠቀው ታጣፊ ክላሽ " የመኪናውን ጎማውን መትቼ ለማስቆም " በሚል በተኮሰው ጥይት የዶ/ር እስራኤል ህይወት ሊያልፍ ችሏል ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስረድቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ አንዳንድ ግዜ ወዲያውኑ መረጃ የማይሰጠው #ከምርመራ_ሂደቱ ጋር በተያያዘ የሚበላሹ ነገሮች ስለሚኖሩ ነው ያለ ሲሆን ቀጣይ የምርመራ መዝገቡ እየታየ መረጃዎችን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የትርታ ኤፍ ኤም 97.6 ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ መሆኑን ያሳውቃል።
* በጉዳዩ ላይ ከሟች ቤተሰቦች / ከቅርብ ጓደኞች መረጃ የሚገኝ ከሆነ ተከታትለን እናቀርባለን።
@tikvahethiopia
😡1.68K😭504❤124😢76🕊32😱31🙏20🥰12👏9