TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል‼️

በአርባምንጭ ከተማ ዛሬ ጠዋት ላይ በደረሰ #የመኪና_አደጋ የ5 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ የአርባምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር #አባሃጅ_ጉጆ እንደገለጹት የካቲት 19/2011 ዓ.ም ጠዋት 2 ሰዓት ላይ በአርባምንጭ ከተማ ወዜ ቀበሌ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3- 53362 ኢት የሆነ ሲኖ ትራክ መኪና እና ኮድ 4-15376 ኢት የሆነ ፒካፕ መኪና ከፍጥነት ወሰን በላይ ሲያሽከረክሩ በተፈጠረ አደጋ እስከ አሁን የ5 ሠዎች ሕይወት አልፏል፡፡

በቦታው ከነበሩ አይን እማኞች በተገኘ መረጃ አደጋው የተፈጠረው በፍጥነት ሲያሽከረክር የነበረው የሲኖ ትራክ አሽከርካሪ ባለ 3 እግር ባጃጅን ለማትረፍ የቀኝ መስመሩን ትቶ ወደ ግራ በመታጠፍ ፒካፕ መኪናን በመግጨት ከመስመር ያስወጣው ሲሆን በእግረኛ መንገድ ስትጓዝ የነበረች የ13 ዓመት ሕጻንን ጨምሮ በፒካፕ መኪናው ውስጥ የነበሩ 3 ተሳፋሪዎች ሕወታቸው አልፏል፡፡

ይሕ በእንዲህ እንዳለ የሲኖ ትራክ አሽከሪው #በፀፀት ራሱን ከመብራት ታዎር ላይ በመጣል ሕይወቱ ማለፉን ም/ኢንስፐክተር አባሃጅ ገልጸው በአደጋው ሁለት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል፡፡

አሽከርካሪዎች ከተፈቀደ ፍጥነት ወሰን በላይ ባለማሽከርከር በሰው ሕይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን አደጋ #መቀነስ እንደሚጠበቅባቸው የከተማው ፖሊስ አዛዥ ም/ኢ/ር አባሃጅ ጉጆ አሳስበዋል፡፡

Via Gamo Zone Administration public Relation office
@tsegabwolde @tikvahethiopia