TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ደብረብርሃን

በደብረ ብርሃን የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው ተብሏል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ትራንስፖርት ልማት ጽ/ቤት ፤ በትራንስፖርት ዘርፍ እየተፈጠረ ያለውን ጫና ለመቅረፍ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን አሳውቋል።

ጽ/ቤቱ በመንግስት ሠራተኛው ላይ የተፈጠረውን የኑሮ ውድነት ጫና ለማቃለል ሠራተኛው ለጊዜው #በነጻ_የትራንስፖረት_አገልግሎት እንዲጠቀም ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል።

የከተማ አውቶብስ አገልግሎት መጀመር በከተማ ታክሲ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ የሚፈጥረው ጫና የለም ተብሏል።

የከተማ አውቶብስ አገልግሎት እንዲጀመር ትራንስፖረት ጽህፈት ቤት ያቀረበውን ዕቅድ የደብረብርሃን ከተማ ከንቲባ ኮሚቴ እና ገንዘብ መምሪያው ተቀብለው ወደ ስራ እንዲገባ መፍቀዳቸው መገለፁን ከከተማው ኮሚኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

@tikvahethiopia
👍1