TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#DrLiaTadesse

በአዲስ አበባ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የሚያዙ ሰዎች ቁጥር መበራከቱን ተከትሎ ምርመራው በስፋት እየተካሄደ መሆኑን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለፁ።

የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በአዲስ አበባ #በኅብረተሰቡ ውስጥ መሰራጨቱ በመረጋገጡ የምርመራ አድማሱን በማስፋት በተለይም በሥራቸው ባህሪይ ለቫይረሱ ተጋላጭ የሆኑ የኀብረተሰብ ክፍሎች ላይ ምርመራው ተጠናክሯል።

በተለይም የቫይረሱ ስርጭት በስፋት በተስተዋለባቸው የአዲስ አበባ ልደታና አዲስ ከተማ ከፍለ ከተሞች እና አካባቢዎች የምርመራ ስራው እየሰፋ መሆኑን ነው ዶክተር ሊያ የተናገሩት።

በከተማዋ የሚደረውን እንቅስቃሴ መዝጋት ሁነኛ መፍትሄ አይደለም ያሉት ሚኒስትሯ ቫይረሱን ለመከላከል የሚወጡ መመሪያዎችን መተግበር ከተቻለ ስርጭቱን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል።

በተጓዳኝም ቫይረሱ በማኅበረሰቡ ውስጥ ያለበትን ደረጃ ማወቅ የሚያስችል የአንቲ ቦዲ ቴስት ወይም ከደም ናሙና በመውሰድ የመመርመር ሥራ በቅርቡ ይጀመራል ብለዋል።

https://telegra.ph/DrLiaTadesse-05-31

#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia