TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ደብረ ታቦር‼️

በደቡብ ጎንደር መስተዳድር ዞን የደብረ ታቦር ማረሚያ ቤት ትላንት ከቀኑ 11፡00 አካባቢ #አለመረጋጋት ተከስቶ ነበር።

ከቀኑ 11፡00 አካባቢ መደበኛው የታራሚዎች ቆጠራ የሚያደርጉ የመምሪያውን የፖሊስ አባላት #በማፈን እስረኞች #ለማምለጥ በመሞከራቸው ነው አለመረጋጋቱ የተፈጠረው።

የፖሊስ አባላቱን በማፈን ግርግር ፈጥረው ለማምለጥ ሙከራ ያደረጉት ደጋጋሚ እስረኞችና ከባድ ፍርደኞች መሆናቸውን የደብረ ታቦር ማረሚያ ቤት መምሪያ ኃላፊ ምክትል ኮማንደር መንጌ ከበደ ተናግረዋል፡፡

የመምሪያ ኃላፊው ለአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት እንዳስታወቁት ተጨማሪ የፖሊስ ኃይል በመጨመር የማረሚያ ቤቱን ሰላም የማረጋጋት ሥራ ተሰርቷል።

ምንጭ፦ አ.ብ.መ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍2