TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ችሎት #Update ከጋራ መኖሪያ ቤቶች ጋር በተያያዘ ከሁለት ሳምንት በፊት በቁጥጥር ስር የዋሉ ስምንት ግለሰቦች ላይ በድጋሚ ለፖሊስ 14 የምርመራ ቀናት ተሰጠ። ለፖሊስ የምርመራ ጊዜውን የሰጠው ዛሬ አርብ ሐምሌ 22/2014 የዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው። የምርመራ ጊዜ የተፈቀደባቸው ተጠርጣሪዎቹ የአዲስ አበባ ከተማ የቴክኒክ ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ…
#ችሎት

ከኮንዶሚኒዬም ዕጣ ማጭበርበር ወንጀል ጋር ተያይዞ በባንክ ሂሳባቸው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ያንቀሳቀሱ ተጠርጣሪ ባለሙያዎች መኖራቸውን ፖሊስ ገለጸ።

ፖሊስ ይህን የገለፀው ተጠርጣሪዎቹን ዛሬ ለ3ኛ ጊዜ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ባቀረበበት ወቅት ነው።

በጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ (ኮንዶሚኒዬም) ዕጣ ከህግ ውጪ ግለሰቦች እንዲካተቱ አድርገዋል ተብለው ከተጠረጠሩ ከ8 የሶፍትዌር ባለሙያዎች መካከል በባንክ ሂሳባቸው ውስጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ያንቀሳቀሱ ተጠርጣሪዎች መኖራቸውን ፖሊስ ለፍ/ቤት ገልጿል።

ቤት ድረስ እየተኬደ በዕጣው የሚገባው ሰው ገንዘብ ይከፍል እንደነበርና ደላላ ተቋቁሞ ከባለሙያ ጋር እየተገናኙ በዕጣው እንዲካተቱ የተደረጉ ግለሰቦች ነበሩ ሲል ፖሊስ ለፍ/ ቤት አስረድቷል። 

በተጨማሪም ፖሊስ ሶፍትዌሩን ካለሙት ባለሙያዎች መካከል ሲስተሙ የማልማት ተግባር በተከናወነበት ጊዜያት ብቻ #በሚስቶቻቸው ሂሳብ ውስጥ በርካታ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በሂሳባቸው ያቀሳቀሱ ተጠርጣሪዎችም እንደነበሩ ማስረጃ ማግኘቱን ጠቅሶ ለችሎት አስረድቷል።

(Credit : Journalist Tarik Adugna)

ያንብቡ :
https://telegra.ph/Condominium-08-12-2
👍490👎81😱39😢3721🙏12👏4