TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ቴላቪቭ‼️

በሺህዎች የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላውያን አንድ #ኢትዮጵያዊ በእስራኤል ፖሊስ መገደሉን በመቃወም ቴላቪቭ ውስጥ ትናንት የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ። የ24 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ይሁዳ ባይድጋ ከሁለት ሳምንት በፊት ነበር በፖሊስ ተተኩሶበት #የተገደለው#ሰልፈኞቹ የቴላቪቭ ዋና ጎዳናን #በመዝጋት እና በዋና ዋና መንገዶች በማለፍ ባካሄዱት ሰልፍ በእሥራኤል ዘረኝነትን እና ፖሊስ የሚፈጽመውን ከመጠን ያለፈ ጥቃት እና አድልዎ #ተቃውመዋል። በእስራኤል ምክር ቤት የሰብአዊ ሐብት ሎጂስቲክ አስተባባሪ አቶ ዮናታን ታከለ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ እንደተናገሩት ኢትዮጵያዊውን የገደለው ፖሊስ አሁንም በስራ ላይ ነው። ይህም ቤተ እስራኤላውያንን በእጅጉ አስቆጥቷል። የዐአእምሮ ህመምተኛው ልጃቸው ይሁዳ ከቤቱ ስለት ይዞ ሲወጣ ፣እንዲደርስላቸው እናቱ ደውለው የነገሩት ፖሊስ ተኩሶ እንደገደለው ተዘግቧል። በእሥራኤል ጦር ውስጥ ማገልገሉ የተነገረውን የይሁዳን አሟሟት የእስራኤል የፍትህ ሚኒስቴር እያጣራሁ ነው ብሏል።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia