TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አቶ ጌታቸው አሰፋ‼️

አቶ #ጌታቸው_አሰፋ በትግራይ ክልል #እንደተሸሸጉ መንግስት መረጃው አለው - ጠቅላይ አቃቢ ህግ
.
.
.
የቀድሞ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አሰፋ በትግራይ ክልል ተሸሽገው እንደሚገኙ መንግሥት መረጃ እንዳለው ነገር ግን እሳቸውን በሕግ ቁጥጥር ሥር ለማዋል ሲባል ጥይት #በመታኮስ የሌላ ሰው ሕይወት እንዲጠፋ ፍላጎት እንደሌላው ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ ለፓርላማ አሳወቁ።

ዋና ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ የመሥሪያ ቤታቸውን የአምስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት፣ በዜጎች ላይ አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዲፈጸም በማድረግ የተጠረጠሩትን አቶ ጌታቸው አሰፋን በሕግ ቁጥጥር ሥር ለማዋል የክልሉ መንግሥት አሳልፎ እንዲሰጥ ጥያቄ ቢቀርብለትም ትብብር ለማድረግ ፈቃደኛ አለመሆኑን ተናግረዋል።

ከአቶ ጌታቸው ውጪ የክልሉ ተወላጅ ያልሆኑ ተጠርጣሪዎችንም ክልሉ ከለላ እንደሰጠና በሕግ ቁጥጥር ሥር ማዋል አለመቻሉን አስረድተዋል። ፓርላማው በዚህ ጉዳይ ላይ አቋም ይዞ ለጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ድጋፍ ሊያደርግ እንደሚገባም ጠይቀዋል።

ይሁን እንጂ አንዳንድ የምክር ቤቱ አባላት በጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ማብራራያ አልተደሰቱም።
መንግሥትም ሆነ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በዚህ ጉዳይ ላይ ፈራ ተባ ሊሉ እንደማይገባ የተናገሩ አንድ የምክር ቤት አባል፣ በደል የፈጸሙ ተጠርጣሪዎችን መንግሥት በሕግ እንዲጠየቁ ማድረግ ሳይችል ስለሕግ የበላይነት ማውራት እንደማይችል ገልጸዋል።

ምንጭ፦ አሀዱ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia