TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሶሳ🔝

በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ግጭት የተጠረጠረን  አንድ ግለሰብ #በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር #ሰይፈዲን_ሃሩን ዛሬ ለኢዜአ እንዳስታወቁት ፖሊስ ሰሞኑን በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በተከሰተው ግጭት ለሶስት ተማሪዎች ሞትና በሌሎችም ለደረሰው ጉዳት የጠረጠረውን አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር አውሏል፡፡

ግለሰቡ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ከዋለ በኋላ “ታምሚያለሁ “ በሚል መድኃኒት ለመውሰድ በጸጥታ ሃይሎች ታጅቦ ወደ መኖሪያ ቤቱ ከሄደ በኋላ በመኖሪያ ቤቱ ያስቀመጠውን መሣሪያ በማቀባበል በጸጥታ ኃይሎች ላይ #ጥቃት ለመፈጸም ሙከራ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡

የግለሰቡ መኖሪያ ቤት ሲፈተሽ የተለያዩ ሀሰተኛ መታወቂያዎች መገኘታቸውን የጠቆሙት ኮሚሽነር ሰይፈዲን የሚጠቀምበትን ኮምፒዩተር ጨምሮ የጸጥታ ሃይሎች ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከረበት ክለሽንኮብ መሣሪያም በቁጥጥር ሥር መዋሉን አስረድተዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲው ግጭት በተጠረጠሩ ሌሎች ግለሰቦች ላይ ፖሊስ ምርመራውን አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል፡፡

በአሶሳ ዩኒቨርስቲ ባለፈው ማክሰኞ ተፈጥሮ በነበረው ግጭት የሶስት ተማሪዎች ህይወት ማለፉና በሌሎች ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱ የሚታወስ ነው፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
ፎቶ፦ TIKVAH-ETH(AB)
@tsegabwolde @tikvahethiopia