TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ይበቃናል‼️

በየዕለቱ አዳዲስ አጀንዳዎችን እየፈጠሩ ወደ ለውጥ፣ ልማት፣ ሰላምና አንድነት የምናደርገውን ጉዞ #እያደናቀፉ ያሉ አካላት አሉ። እነዚህን ቀንደኛ የሀገር ጠላቶች እና የጥፋት ሀይሎች አምርረን #ልንታገላቸው ይገባናል።

በቃን! በቃን! በቃን! ለብዙ አመታት በጦርነት ተሰቃይተናል፣ ሰዎች ገብረናል፣ ችግር አይተናል፣ ረሀብ ተፈራርቆብናል፣ ድህነት መጠሪያችን ሆኗል፣ ስማችን በዓለም ተዋርዷል፣ የሌላ ሀገር መሬትን ተመኝተን ባህር ገብተን ሞተናል፣ የበረሀ ሲሳይ ሆነናል፣ እርስ በእርሳችን እየተጋጨን የድህነትን ኑሮ ገፍተናል ወገኖቼ አሁን ግን ይበቃናል!!

•ችግሩ ይበቃናል
•ጥላቻው ይበቃናል
•ተንኮሉ ይበቃናል
•ሞቱ ይበቃናል
•ረሀቡ ይበቃናል
•መፈናቀሉ ይበቃናል
•ለቅሶው ይበቃናል
•ለመኖር መስጋቱ ይበቃናል
•ወጥቶ ለመግባት #መፍራቱ ይበቃናል

ኑ ያለፈውን ትተን ለመጪው እንስራ። ኑ ታላቅ እንሁን። ለኛ እንኳን ባይሆን ለልጅ ልጆቻችን ስንል ጠንካራ ሀገር #ገንብተን እንለፍ። ምንም ባናወርስ #ፍቅሯ#አንድነቷ#ሰላሟ የተረጋገጠች ሀገር እናውርስ!

አመሰግናለሁ!
ፀጋአብ ወልዴ
@tsegabwolde @tikvahethiopia