TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#መደመር

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ”መደመር” በሚል ርዕስ ያዘጋጁት አዲስ መጽሐፍ በሳምንታት ጊዜ ውስጥ በአማርኛ እና በኣፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች ለገበያ እንደሚውል ተሰምቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር ፍልስፍና ይዘው ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ጽፈውታል የተባለው ይህ መጽሐፍ ህትመቱ የተጠናቀቀ ሲሆን ገቢው በገጠር ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች ይውላል። በሦስት መቶ ብር ወይም በ 30 የአሜሪካን ዶላር ለገበያ የሚውለው ይህ መጽሐፍ 365 ገፆች ሲኖሩት በ16 ምዕራፎች የተከፋፈለ ነው።

Via #ADDISMALEDA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#መደመር_መጽሐፍ
#በድሬዳዋ
#ዛሬ_ይመረቃል

በዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የተፃፈው ‘’መደመር ’’ መጽሐፍ ዛሬ ጥቅምት 8 በኢትዮጵያና በአሜሪካ በሚገኙ 20 ከተሞች የሚመረቅ ሲሆን ድሬዳዋም የዚህው መረዓ ግብር አንዱ አካል ነች። በመደመር መጽሐፍ በአማርኛ ፣ ኦሮምኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች የተፃፈ እንዲሁም አንድ ሚሊዮን ቅጂዎችም የታተመ ሲሆን ይህ መጽሐፉ 300 ብር ዋጋ የተቆረጠለት እና ከሽያጩ የሚገኘው ገቢም በአገሪቷ ላሉ ትምህርት ቤት ግንባታ ይውላል ተብሏል። በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ በመጽሐፉ ይዘት ዙሪያ ማብራሪያና ትንተና ይሰጥበታልም ተብሎ ይጠበቃል።

PHOTO: #ተርቢኖስ_ዘደብረ_ሃይል
@tsegabwolde @tikvahethiopia