TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የ˝ፀረ- ጥላቻ ንግግር˝ን አዋጅ አያረቀቀ ነዉ፦

ጠቅላይ አቃቤ ህግ ከ˝ፀረ ጥላቻ ንግግር˝ አዋጅ በተጨማሪ በርካታ ህጎችን በማሻሻል ላይ እንደሚገኝ ተሰምቷል፡፡ በጠቅላይ አቃቤ ህግ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዝናቡ ቱኑ እንደተናገሩት የ˝ፀረ ጥላቻ ንግግር˝ አዋጅን የሰዎችን የመናገር ነፃነት #ሊገድብ በማይችል መልኩ እና ከህግ መንግስቱ ጋር #ሊጋጭ በማይችል መልኩ ለማፅደቅ አስፈላጊ ጥናቶች ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ ከሌሎች ህጎች ፈጥኖ የሚጸድቀው ይህ ˝የፀረ ጥላቻ ንግግር˝ አዋጅ ኢትዮጵያ ላይ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ብሄሮች እና ማንነቶች ላይ በጥላቻ ንግግር ምክንያት የሚደርሰውን ችግር እና ግጭት ለማስቀረት እንደሚያግዝ አቶ ዝናቡ ተናግረዋል፡፡

Via Arts TV World
@tsegabwolde @tikvahethiopia