አዲስ አበባ‼️
በጉለሌ ክ/ከተማ በህገወጥ መንገድ ተይዘው የነበሩ 120 የቀበሌ ቤቶችና 64 ሼዶች #ለችግረኞች ተሰጡ።
ከህብረተሰቡ የተወጣጡ ከ200 በላይ አባላት ያሉት ኮሚቴ የሚደርሰውን ጥቆማ በማጥራት በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ ቤቶችን ለማስለቀቅ እየሰራ መሆኑን የክፍለከተማው የስራ ሀላፊዎች ገልፀዋል።
የማህበረሰቡን ተጠቃሚነትና ፍትሀዊነትን ለማረጋገጥ በክፍለከተማው ከተገኙት 120 ቤቶች 53 ቤቶች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ነዋሪዎች የተላለፉ ሲሆን ቀሪዎቹ ቤቶች ለልማት ተነሺዎች ተሰጥተዋል።
በተመሳሳይ በክፍለ ከተማው ያላግባብ ተይዘው የነበሩ የጥቃቅንና አነስተኛ መስሪያ ቦታዎችን በማስለቀቅ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ ተደራጅተው በመስሪያ ቦታ እጦት ወደ ስራ ላልገቡ ወጣቶችና ሴቶች ተሰጥተዋል፡፡
በተጨማሪም ኢ-መደበኛ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊነት በማምጣት ለ1046 ነዋሪዎች በክፍለከተማው ባሉ 5 ሳይቶች ቦታ በማመቻቸት ወደ ስራ የሚገቡበት ሁኔታም ተመቻችቷል፡፡
ምንጭ፡- የከንቲባ ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በጉለሌ ክ/ከተማ በህገወጥ መንገድ ተይዘው የነበሩ 120 የቀበሌ ቤቶችና 64 ሼዶች #ለችግረኞች ተሰጡ።
ከህብረተሰቡ የተወጣጡ ከ200 በላይ አባላት ያሉት ኮሚቴ የሚደርሰውን ጥቆማ በማጥራት በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ ቤቶችን ለማስለቀቅ እየሰራ መሆኑን የክፍለከተማው የስራ ሀላፊዎች ገልፀዋል።
የማህበረሰቡን ተጠቃሚነትና ፍትሀዊነትን ለማረጋገጥ በክፍለከተማው ከተገኙት 120 ቤቶች 53 ቤቶች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ነዋሪዎች የተላለፉ ሲሆን ቀሪዎቹ ቤቶች ለልማት ተነሺዎች ተሰጥተዋል።
በተመሳሳይ በክፍለ ከተማው ያላግባብ ተይዘው የነበሩ የጥቃቅንና አነስተኛ መስሪያ ቦታዎችን በማስለቀቅ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ ተደራጅተው በመስሪያ ቦታ እጦት ወደ ስራ ላልገቡ ወጣቶችና ሴቶች ተሰጥተዋል፡፡
በተጨማሪም ኢ-መደበኛ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊነት በማምጣት ለ1046 ነዋሪዎች በክፍለከተማው ባሉ 5 ሳይቶች ቦታ በማመቻቸት ወደ ስራ የሚገቡበት ሁኔታም ተመቻችቷል፡፡
ምንጭ፡- የከንቲባ ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia