TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ቴፒ‼️

በደቡብ ክልል በቴፒ ከተማ #ለተቃዉሞ አደባባይ በወጡ ወጣቶች ላይ ፀጥታ አስከባሪዎች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ አራት ሰዎች ተገደሉ። ሌሎች ሰባት ቆሰሉ። የዐይን ምስክሮች እንዳሉት ከሟቾቹ አንዱ የአስራ ሶስት ዓመት ታዳጊ ወጣት ነዉ ተብሏል። የጀርመን ድምፅ ራድዮ የከተማይቱን ነዋሪዎች ጠቅሶ እንደዘገበዉ ከግጭቱ በኋላ የከተማይቱ የንግድ፣ የትራንስፖርትና የመንግሥት መስሪያቤቶች እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ #ተቋርጧል። ፀጥታ አስከባሪዎች የከተማይቱን ዋና ዋና መንገዶችን በጥብቅ እየተቆጣጠሩ ነዉ። የቴፒና የአካባቢዋ ነዋሪዎች የራስ አስተዳደር ጥያቄ በማንሳት አደባባይ መዉጣት ከጀመሩ ካለፈዉ ጥቅምት ጀምሮ ነዋሪዎችና ፀጥታ አስከባሪዎች በተደጋጋሚ ይጋጫሉ። በየግጭቱ የሰዉ ሕይወት ይጠፋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia