TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኦቦ ዳውድ ኢብሳ⬇️

በሀገሪቱ አየታየ ያለው ለውጥ እንዳይደናቀፍ ጥያቄዎች #በሰላማዊ መንገድ ሊቀርቡ አንደሚገባ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ገልጸዋል።

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ #ዳውድ_ኢብሳ ከfbc ጋር በነበራቸው ቆይታ ለውጡ እንደዚህ ቀደም ለውጦች በጅምር እንዳይቀር ሁሉም የየበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

በተለይም ወጣቱ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎችንም ሆነ ቅሬታዎች ሲገልጽ፥ ህግና ስርዓትን በተከተለና የሌሎችን መብት በማክበር ብቻ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ይህ ካልሆነ ብዙ #መስዋትነት የተከፈለበት ለውጥ ከግቡ ሳይደርሰ ሊጨናገፈና ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ ሊወስድ እንደሚችል ነው አቶ ዳውድ የተናገሩት።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ወደ ሀገር የገባውም #ልዩነትን ለማጥፋት እንዳልሆነ የገለጹት ሊቀመንበሩ የሰው ልጆች እስካሉ ድረስ ልዩነቶች መኖራቸውንም አስረድተዋል።

ይሁን እንጂ ልዩነቶን #ለማጥበብ በተረጋጋ መንፈስና በሰከነ አካሄድ ውይይቶችን ማድረግ እደሚየስፈልግ ተናግረዋል ተናግረዋል።

ሰውን #በመግደልና ንብረትን በማውደም ልዩነት ይሰፋል እንደሆነ እንጂ የማይጠብ መሆኑንም ያመላከቱት የግንባሩ ሊቀመነበር ይህንን አይነት ድርጊት መቼም ቢሆን ድርጅታቸው የማይደግፍና የማይቀበል መሆኑን አስገንዝበዋል።

አብዛኛው ህዝብ ለውጡን እንደሚፈልገው የተናገሩት የኦሮሞ ነጻነት ግናባር የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

እንደ አቶ ዳውድ ገለጻ አብዛኛው ህዝብ ለውጡን እንደሚፈልገው ሲሆን፥ የኦሮሞ ነጻነት ግናባር እና ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

መስዋትነት የተከፈለውም የሰባዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ለማስከበርና ለመስጠበቅ መሆኑንም አመላክተዋል።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia